1Aš išvydau dar vieną galingą angelą, nužengiantį iš dangaus, apsisiautusį debesimi. Jo galvą supo vaivorykštė, veidas švytėjo kaip saulė ir kojostarsi ugnies stulpai.
1ሌላም ብርቱ መልአክ ደመና ተጐናጽፎ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ በራሱም ላይ ቀስተ ደመና ነበረ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ እግሮቹም እንደ እሳት ዓምዶች ነበሩ፥
2Jis laikė rankoje išvyniotą knygelę. Ir Jis atsistojo dešiniąja koja ant jūros, o kairiąja ant sausumos,
2የተከፈተችንም ታናሽ መጽሐፍ በእጁ ያዘ። ቀኝ እግሩንም በባሕር ላይ ግራውንም በምድር ላይ አኖረ፥ እንደሚያገሣም አንበሳ በታላቅ ድምፅ ጮኸ።
3ir ėmė šaukti galingu balsu tartum riaumojantis liūtas. Kai jis sušuko, atsiliepė septyni griaustiniai savais balsais.
3በጮኸም ጊዜ ሰባቱ ነጐድጓድ በየድምፃቸው ተናገሩ።
4Septyniems griaustiniams prabilus savais balsais, puoliausi rašyti, bet išgirdau iš dangaus balsą, sakantį man: “Užantspauduok, ką pasakė septyni griaustiniai, ir to nerašyk!”
4ሰባቱ ነጐድጓድ በተናገሩ ጊዜ ልጽፍ አሰብሁ፤ ከሰማይም። ሰባቱ ነጐድጓድ የተናገሩትን ነገር በማኅተም ዝጋው አትጻፈውም የሚል ድምፅ ሰማሁ።
5O angelas, kurį mačiau stovint ant jūros ir ant sausumos, pakėlė savo ranką į dangų
5በባሕርና በምድርም ላይ ሲቆም ያየሁት መልአክ ቀኝ እጁን ወደ ሰማይ አሻቅቦ ዘረጋ፥
6ir prisiekė Gyvenančiuoju per amžių amžius, kuris sutvėrė dangų ir visa, kas jame, žemę ir visa, kas joje, bei jūrą ir visa, kas joje,kad laiko daugiau nebebus,
6ሰማይንና በእርሱም ያሉትን፥ ምድርንና በእርስዋም ያሉትን፥ ባሕርንና በእርሱም ያሉትን በፈጠረው፥ ከዘላለምም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ሆኖ በሚኖረው ምሎ።
7bet septintojo angelo trimitavimo dienomis bus baigta Dievo paslaptis, kaip Jis yra paskelbęs Gerąją naujieną savo tarnams pranašams.
7ወደ ፊት አይዘገይም፥ ዳሩ ግን ሰባተኛው መልአክ ሊነፋ ባለው ጊዜ ድምፁም በሚሰማበት ዘመን፥ ለባሪያዎቹ ለነቢያት የምስራች እንደ ሰበከላቸው የእግዚአብሔር ምሥጢር ይፈጸማል አለ።
8Tuomet balsas, kurį girdėjau iš dangaus, vėl ėmė kalbėti man ir tarė: “Eik, paimk atvyniotą knygelę iš angelo rankos, stovinčio ant jūros ir sausumos”.
8ከሰማይም የሰማሁት ድምፅ እንደ ገና ሲናገረኝና። ሂድና በባሕርና በምድር ላይ ከሚቆመው መልአክ በእጁ ያለችውን የተከፈተችውን መጽሐፍ ውሰድ ሲል ሰማሁ።
9Aš nuėjau pas angelą ir paprašiau, kad duotų man knygelę. O jis man tarė: “Imk ir suvalgyk ją! Ji bus karti viduriuose, bet burnoje ji bus saldi kaip medus”.
9ወደ መልአኩም ሄጄ። ታናሺቱን መጽሐፍ ስጠኝ አልሁት። እርሱም። ውሰድና ብላት፥ ሆድህንም መራራ ታደርገዋለች በአፍህ ግን እንደ ማር ትጣፍጣለች አለኝ።
10Ir aš paėmiau knygelę iš angelo rankos ir ją suvalgiau. Ji buvo mano burnoje saldi tarytum medus, bet kai prarijau, mano viduriuose ji apkarto.
10ከመልአኩም እጅ ታናሺቱን መጽሐፍ ወስጄ በላኋት በአፌም እንደ ማር ጣፋጭ ሆነች፤ ከበላኋት በኋላም ሆዴ መራራ ሆነ።
11Ir jis pasakė man: “Tu turi vėl pranašauti apie daugelį žmonių, tautų, kalbų ir karalių”.
11በብዙ ወገኖችና በአሕዛብም በቋንቋዎችም በነገሥታትም ላይ እንደ ገና ትንቢት ትናገር ዘንድ ይገባሃል ተባለልኝ።