1Ir sutrimitavo penktasis angelas. Aš išvydau žvaigždę, nukritusią iš dangaus žemėn. Jai buvo duotas raktas nuo bedugnės šulinio.
1አምስተኛውም መልአክ ነፋ፤ ከሰማይም ወደ ምድር ወድቆ የነበረ ኮከብ አየሁ፥ የጥልቁም ጕድጓድ መክፈቻ ተሰጠው።
2Ji atidarė bedugnės šulinį, ir išsiveržė dūmai iš šulinio, tarytum iš milžiniškos krosnies. Ir aptemo saulė ir oras nuo šulinio dūmų,
2የጥልቁንም ጕድጓድ ከፈተው፤ ጢስም ከታላቅ እቶን እንደሚወጣ ጢስ ሆኖ ከጕድጓዱ ወጣ ፀሐይና አየርም በጕድጓዱ ጢስ ጨለሙ።
3o iš dūmų pasipylė žemėn skėriai, kuriems buvo duota galia, kaip turi galią žemės skorpionai.
3ከጢሱም አንበጣዎች ወደ ምድር ወጡ፥ የምድርም ጊንጦች ሥልጣን እንዳላቸው ሥልጣን ተሰጣቸው።
4Jiems buvo įsakyta nekenkti žemės žolei, nei jokiam žalumynui, nei jokiam medžiui, o vien tik žmonėms, kurie neturi savo kaktose Dievo antspaudo.
4የእግዚአብሔርም ማኅተም በግምባራቸው ከሌለባቸው ሰዎች በቀር በምድር ያለውን ሣር ቢሆንም ወይም ማናቸውንም የለመለመ ነገር ወይም ማናቸውንም ዛፍ እንዳይጐዱ ተባለላቸው።
5Ir jiems buvo leista ne žudyti žmones, bet kankinti penkis mėnesius; jų kankinimas it kankinimas skorpiono, kai jis įgelia žmogų.
5አምስትም ወር ሊሣቅዩአቸው ተሰጣቸው እንጂ ሊገድሉአቸው አይደለም፤ እነርሱም የሚሣቅዩት ሥቃይ ጊንጥ ሰውን ነድፎ እንደሚሣቅይ ነው።
6Anomis dienomis žmonės ieškos mirties ir jos neras, trokš numirti, bet mirtis bėgs nuo jų.
6በዚያም ወራት ሰዎች ሞትን ይፈልጋሉ አያገኙትምም፥ ሊሞቱም ይመኛሉ ሞትም ከእነርሱ ይሸሻል።
7Skėrių išvaizda panaši į žirgų, parengtų kautynėms. Ant jų galvų tartum vainikai, panašūs į auksą, o jų veidaitartum žmonių veidai;
7የአንበጣዎቹም መልክ ለጦርነት እንደ ተዘጋጁ ፈረሶች ነው፥ በራሳቸውም ላይ ወርቅ እንደሚመስሉ አክሊሎች ነበሩአቸው፥ ፊታቸውም እንደ ሰው ፊት ነበረ፤
8jie turėjo plaukus, panašius į moterų plaukus, o jų dantys buvo lyg liūtų dantys.
8የሴቶችን ጠጕር የሚመስል ጠጕር ነበራቸው፥ ጥርሳቸውም እንደ አንበሳ ጥርስ ነበረ፥
9Jie turėjo šarvus tarsi geležinius krūtinšarvius, o jų sparnų garsas buvo kaip bildesys daugybės vežimų ir arklių, bėgančių į mūšį.
9የብረት ጥሩር የሚመስልም ጥሩር ነበራቸው፥ የክንፋቸውም ድምፅ ወደ ጦርነት እንደሚጋልቡ እንደ ብዙ ፈረሶች ሰረገላዎች ድምፅ ነበረ።
10Jie turi uodegas, panašias į skorpionų, ir geluonis uodegose. Jie turi valdžią kenkti žmonėms per penkis mėnesius.
10እንደ ጊንጥም ጅራት ያለ ጅራት አላቸው በጅራታቸውም መውጊያ አለ፥ ሰዎችንም አምስት ወር እንዲጐዱ ሥልጣን አላቸው።
11Jie turi sau karalių, bedugnės angelą, kurio vardas hebrajiškai Abadonas, o graikiškai tas vardas Apolionas.
11በእነርሱም ላይ ንጉሥ አላቸው እርሱም የጥልቅ መልአክ ነው፥ ስሙም በዕብራይስጥ አብዶን በግሪክም አጶልዮን ይባላል።
12Pirmoji neganda praėjo; štai iš paskos eina dar dvi negandos.
12ፊተኛው ወዮ አልፎአል፤ እነሆ፥ ከዚህ በኋላ ገና ሁለት ወዮ ይመጣል።
13Ir sutrimitavo šeštasis angelas. Aš išgirdau balsą nuo keturių ragų auksinio aukuro, stovinčio Dievo akivaizdoje.
13ስድስተኛውም መልአክ ነፋ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ካለ በወርቅ ከተሠራ መሠዊያ ቀንዶች አንድ ድምፅ ሰማሁ፥
14Jis sakė šeštajam angelui, turinčiam trimitą: “Paleisk keturis angelus, kurie yra surišti prie didžiosios Eufrato upės!”
14መለከትም ያለውን ስድስተኛውን መልአክ። በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ የታሰሩትን አራቱን መላእክት ፍታቸው አለው።
15Ir buvo atrišti keturi angelai, paruošti nustatytai valandai, dienai, mėnesiui ir metams išžudyti trečdalį žmonių.
15የሰዎችንም ሲሶ እንዲገድሉ ለሰዓቱና ለቀኑ ለወሩም ለዓመቱም ተዘጋጅተው የነበሩ አራቱ መላእክት ተፈቱ።
16Jų kariuomenės skaičius,aš išgirdau skaičių,buvo du miriadai miriadų.
16የፈረሰኞችም ጭፍራ ቁጥር እልፍ ጊዜ እልፍ፥ እልፍ ጊዜ እልፍ ነበረ፤ ቁጥራቸውን ሰማሁ።
17Taigi aš mačiau regėjime žirgus ir raitelius su krūtinšarviais, ugniaspalviais, violetiniais ir geltonais; žirgų galvos atrodė kaip liūtų galvos, o iš jų nasrų veržėsi ugnis, dūmai ir siera.
17ፈረሶቹንና በእነርሱም ላይ የተቀመጡትን እንዲሁ በራእይ አየሁ፤ እሳትና ያክንት ዲንም የሚመስል ጥሩር ነበራቸው፤ የፈረሶቹም ራስ እንደ አንበሳ ራስ ነበረ፥ ከአፋቸውም እሳትና ጢስ ዲንም ወጣ።
18Trečdalis žmonių žuvo nuo šitų trijų piktenybiųnuo ugnies, dūmų ir sieros, besiveržiančių iš jų nasrų.
18ከአፋቸውም በወጡት በእሳቱና በጢሱ በዲኑም በእነዚህ ሦስት መቅሰፍቶች የሰዎቹ ሲሶ ተገደለ።
19Mat jų galia buvo jų nasruose ir jų uodegose. Jų uodegos panašios į gyvates ir turi galvas, kuriomis kenkia.
19የፈረሶቹ ሥልጣን በአፋቸውና በጅራታቸው ነውና፤ ጅራታቸው እባብን ይመስላልና፥ ራስም አላቸው በእርሱም ይጐዳሉ።
20Bet likusieji žmonės, kurie nebuvo šitų piktenybių išžudyti, neatgailavo dėl savo rankų darbų, kad nebegarbintų demonų ir auksinių, sidabrinių, žalvarinių, akmeninių ir medinių stabų, kurie negali nei matyti, nei girdėti, nei vaikščioti.
20በእነዚህም መቅሠፍቶች ያልተገደሉት የቀሩቱ ሰዎች ለአጋንንትና ያዩ ወይም ይሰሙ ወይም ይሄዱ ዘንድ ለማይችሉ ከወርቅና ከብር ከናስም ከድንጋይም ከእንጨትም ለተሠሩ ለጣዖቶች እንዳይሰግዱ ስለ እጃቸው ሥራ ንስሐ አልገቡም፤
21Jie taip pat neatgailavo dėl savo žmogžudysčių, žyniavimų, ištvirkavimų ir vagysčių.
21ስለ መግደላቸውም ቢሆን ወይም ስለ አስማታቸው ወይም ስለ ዝሙታቸው ወይም ስለ ስርቆታቸው ንስሐ አልገቡም።