Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

8

1Kai Avinėlis atplėšė septintąjį antspaudą, danguje pusvalandžiui pasidarė tylu.
1ሰባተኛውንም ማኅተም በፈታ ጊዜ እኵል ሰዓት የሚያህል ዝምታ በሰማይ ሆነ።
2Ir aš išvydau septynis angelus, stovinčius Dievo akivaizdoje, ir jiems buvo įteikti septyni trimitai.
2በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው።
3Atėjo dar vienas angelas ir atsistojo prie aukuro, laikydamas aukso smilkytuvą. Jam buvo duota daug smilkalų, kad jis aukotų juos su visų šventųjų maldomis ant auksinio aukuro priešais sostą.
3ሌላም መልአክ መጣና የወርቅ ጥና ይዞ በመሰዊያው አጠገብ ቆመ፤ በዙፋኑም ፊት ባለው በወርቅ መሰዊያ ላይ ለቅዱሳን ሁሉ ጸሎት እንዲጨምረው ብዙ ዕጣን ተሰጠው።
4Ir pakilo smilkalų dūmai su šventųjų maldomis iš angelo rankų Dievo akivaizdon.
4የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ።
5Po to angelas paėmė smilkytuvą, pripildė jį aukuro ugnies ir sviedė į žemę. Sugriaudė griausmai, pakilo šauksmai, sublyksėjo žaibai, sudrebėjo žemė.
5መልአኩም ጥናውን ይዞ የመሰዊያውን እሳት ሞላበት ወደ ምድርም ጣለው፤ ነጐድጓድና ድምፅም መብረቅም መናወጥም ሆነ።
6Septyni angelai, turintys septynis trimitus, pasiruošė trimituoti.
6ሰባቱንም መለከት የያዙ ሰባቱ መላእክት ሊነፉ ተዘጋጁ።
7Sutrimitavo pirmasis angelas. Ir radosi kruša ir ugnis, sumišę su krauju, ir tai buvo numesta žemėn. Ir išdegė trečdalis medžių ir visa žaliuojanti žolė.
7ፊተኛውም መልአክ ነፋ፤ ደምም የተቀላቀለበት በረዶና እሳት ሆነ፥ ወደ ምድርም ተጣለ፤ የምድርም ሲሶው ተቃጠለ የዛፎችም ሲሶው ተቃጠለ የለመለመም ሣር ሁሉ ተቃጠለ።
8Sutrimitavo antrasis angelas. Ir tarytum didžiulis kalnas, liepsnojantis ugnimi, buvo sviestas į jūrą, ir trečdalis jūros pavirto krauju.
8ሁለተኛውም መልአክ ነፋ፤ በእሳት የሚቃጠል ታላቅ ተራራን የሚመስል ነገር በባሕር ተጣለ፤ የባሕርም ሲሶው ደም ሆነ
9Trečdalis jūros padarų, turinčių gyvybę, išdvėsė, ir trečdalis laivų buvo sunaikinti.
9በባሕርም ከሚኖሩ ሕይወት ካላቸው ፍጥረቶች ሲሶው ሞተ የመርከቦችም ሲሶው ጠፋ።
10Ir sutrimitavo trečiasis angelas. Tada iš dangaus nukrito didelė žvaigždė, liepsnodama tarsi deglas, ir nukrito ant trečdalio upių ir ant vandens šaltinių.
10ሦስተኛውም መልአክ ነፋ፤ እንደ ችቦም የሚቃጠል ታላቅ ኮከብ ከሰማይ ወደቀ፥ በወንዞችና በውኃም ምንጮች ሲሶ ላይ ወደቀ። የኮከቡም ስም እሬቶ ይባላል።
11Žvaigždės vardas yra Metėlė. Ir pavirto trečdalis vandenų į metėlę, ir daugybė žmonių mirė nuo vandens, nes jis pasidarė kartus.
11የውኃውም ሲሶ መራራ ሆነ መራራም ስለተደረገ በውኃው ጠንቅ ብዙ ሰዎች ሞቱ።
12Ir sutrimitavo ketvirtasis angelas. Tuomet buvo užgautas trečdalis saulės, trečdalis mėnulio ir trečdalis žvaigždžių taip, kad jų trečdalis užtemo. Diena bei naktis prarado trečdalį šviesumo.
12አራተኛውም መልአክ ነፋ፤ የፀሐይ ሲሶና የጨረቃ ሲሶ የከዋክብትም ሲሶ ተመታ፥ የእነዚህ ሲሶ ይጨልም ዘንድ፥ የቀንም ሲሶው እንዳያበራ፥ እንዲሁም የሌሊት።
13Aš regėjau ir girdėjau dangaus viduriu lekiantį angelą, kuris garsiu balsu skelbė: “Vargas, vargas, vargas žemės gyventojams nuo besirengiančių užtrimituoti kitų trijų angelų trimitų garsų!”
13አየሁም፥ አንድም ንስር በሰማይ መካከል እየበረረ በታላቅ ድምፅ። ሊነፉ ያላቸው የሦስቱ መላእክት መለከት ስለሚቀረው ድምፅ በምድር ላይ ለሚኖሩት ወዮላቸው፥ ወዮላቸው፥ ወዮላቸው ሲል ሰማሁ።