Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

7

1Po to aš regėjau keturis angelus, stovinčius keturiuose žemės kampuose, laikančius keturis žemės vėjus, kad vėjas nepūstų nei žemėje, nei jūroje, nei į medžius.
1ከዚህም በኋላ በአራቱ በምድር ማዕዘን ቆመው አራት መላእክት አየሁ፥ እነርሱም ነፋስ በምድር ቢሆን ወይም በባሕር ወይም በማንም ዛፍ እንዳይነፍስ አራቱን የምድር ነፋሳት ያዙ።
2Ir išvydau kitą angelą, pakylantį nuo saulėtekio, turintį gyvojo Dievo antspaudą. Jis šaukė skardžiu balsu keturiems angelams, kuriems buvo duota kenkti žemei ir jūrai:
2የሕያው አምላክ ማኅተም ያለውም ሌላ መልአክ ከፀሐይ መውጫ ሲወጣ አየሁ፥ ምድርንና ባሕርንም ሊጐዱ ለተሰጣቸው ለአራቱ መላእክት በታላቅ ድምፅ እየጮኸ።
3“Nekenkite nei žemei, nei jūrai, nei medžiams, kol paženklinsime antspaudu savo Dievo tarnų kaktas!”
3የአምላካችንን ባሪያዎች ግምባራቸውን እስክናትማቸው ድረስ ምድርን ቢሆን ወይም ባሕርን ወይም ዛፎችን አትጕዱ አላቸው።
4Ir aš išgirdau paženklintųjų skaičių: šimtas keturiasdešimt keturi tūkstančiai paženklintųjų iš visų Izraelio vaikų giminių:
4የታተሙትንም ቍጥር ሰማሁ፤ ከእስራኤል ልጆች ነገድ ሁሉ የታተሙት መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ።
5Iš Judo giminės dvylika tūkstančių paženklintųjų, iš Rubeno giminės dvylika tūkstančių, iš Gado giminės dvylika tūkstančių,
5ከይሁዳ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ታተሙ፥ ከሮቤል ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከጋድ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥
6iš Asero giminės dvylika tūkstančių, iš Neftalio giminės dvylika tūkstančių, iš Manaso giminės dvylika tūkstančių,
6ከአሴር ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከንፍታሌም ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥
7iš Simeono giminės dvylika tūkstančių, iš Levio giminės dvylika tūkstančių, iš Isacharo giminės dvylika tūkstančių,
7ከምናሴ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከስምዖን ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከሌዊ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከይሳኮር ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥
8iš Zabulono giminės dvylika tūkstančių, iš Juozapo giminės dvylika tūkstančių, iš Benjamino giminės dvylika tūkstančių paženklintųjų.
8ከዛብሎን ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከዮሴፍ ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ፥ ከብንያም ነገድ አሥራ ሁለት ሺህ ታተሙ።
9Paskui regėjau: štai milžiniška minia, kurios niekas negalėjo suskaičiuoti, iš visų giminių, genčių, tautų ir kalbų. Visi stovėjo priešais sostą ir Avinėlį, apsisiautę baltais apsiaustais, su palmių šakomis rankose.
9ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤
10Jie šaukė skambiu balsu: “Išgelbėjimas iš mūsų Dievo, sėdinčio soste, ir Avinėlio!”
10በታላቅም ድምፅ እየጮሁ። በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው ለአምላካችንና ለበጉ ማዳን ነው አሉ።
11Visi angelai, stovintys aplink sostą, vyresniuosius ir keturias būtybes, parpuolė prieš sostą veidais žemėn ir pagarbino Dievą,
11መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ በአራቱም እንስሶቹ ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑም ፊት በግምባራቸው ተደፉ፥ ለእግዚአብሔርም እየሰገዱ።
12sakydami: “Amen! Palaiminimas, ir šlovė, ir išmintis, ir padėka, ir garbė, ir jėga, ir galybė mūsų Dievui per amžių amžius! Amen!”
12አሜን፥ በረከትና ክብር ጥበብም ምስጋናም ውዳሴም ኃይልም ብርታትም ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ለአምላካችን ይሁን፤ አሜን አሉ።
13Tuomet vienas iš vyresniųjų tarė man: “Kas tokie yra ir iš kur atėjo tie, apsivilkę baltais apsiaustais?”
13ከሽማግሌዎቹም አንዱ ተመልሶ። እነዚህ ነጩን ልብስ የለበሱ እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ? አለኝ።
14Aš jam atsakiau: “Viešpatie, tu žinai”. Ir jis man tarė: “Jie atėjo iš didelio suspaudimo. Jie išplovė savo apsiaustus ir juos išbaltino Avinėlio kraujyje.
14እኔም። ጌታ ሆይ፥ አንተ ታውቃለህ አልሁት። አለኝም። እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፥ ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ።
15Todėl jie yra prieš Dievo sostą ir tarnauja Jam dieną ir naktį Jo šventykloje, o Sėdintysis soste išskleis ant jų savo palapinę.
15ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ፥ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል፥ በዙፋኑም ላይ የተቀመጠው በእነርሱ ላይ ያድርባቸዋል።
16Jie daugiau nebealks ir nebetrokš, nebekepins jų saulė nei jokia kaitra.
16ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም፥ ከእንግዲህም ወዲህ አይጠሙም፥ ፀሐይም ትኵሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም፤
17Nes Avinėlis, kuris sosto viduryje, juos ganys ir vedžios prie gyvųjų vandens šaltinių, ir Dievas nušluostys kiekvieną ašarą nuo jų akių”.
17በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና፥ ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና፤ እግዚአብሔርም እንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።