Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

14

1Ir aš išvydau: štai Avinėlis, bestovįs ant Siono kalno, o su Juo šimtas keturiasdešimt keturi tūkstančiai, turintys Jo Tėvo vardą, įrašytą savo kaktose.
1አየሁም፥ እነሆም፥ በጉ በጽዮን ተራራ ቆሞ ነበር፥ ከእርሱም ጋር ስሙና የአባቱ ስም በግምባራቸው የተጻፈላቸው መቶ አርባ አራት ሺህ ነበሩ።
2Aš išgirdau iš dangaus garsą, tarsi daugybės vandenų šniokštimą ir tarsi galingo griaustinio dundėjimą. Garsas, kurį girdėjau, buvo tarytum arfininkų, skambinančių savo arfomis.
2እንደ ብዙ ውኃም ድምፅና እንደ ታላቅ ነጐድጓድ ድምፅ ያለ ከሰማይ ድምፅን ሰማሁ፥ ደርዳሪዎችም በገና እንደሚደረድሩ ያለ ድምፅ ሰማሁ።
3Jie giedojo naują giesmę priešais sostą, keturias būtybes ir vyresniuosius, ir niekas negalėjo išmokti tos giesmės, išskyrus tuos šimtą keturiasdešimt keturis tūkstančius, atpirktus iš žemės.
3በዙፋኑም ፊት በአራቱም እንስሶችና በሽማግሌዎቹ ፊት አዲስ ቅኔ ዘመሩ፤ ከምድርም ከተዋጁት ከመቶ አርባ አራት ሺህ በቀር ያን ቅኔ ሊማር ለማንም አልተቻለውም።
4Tai tie, kurie nesusitepė su moterimis, nes jie mergelės. Tai tie, kurie lydi Avinėlį, kur tik Jis eina. Jie yra atpirkti iš žmonių, pirmieji vaisiai Dievui ir Avinėliui.
4ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው፥ ድንግሎች ናቸውና። በጉ ወደሚሄድበት የሚከተሉት እነዚህ ናቸው። ለእግዚአብሔርና ለበጉ በኵራት እንዲሆኑ ከሰዎች የተዋጁ እነዚህ ናቸው።
5Jų lūpose nerasta apgaulės; jie be dėmės prieš Dievo sostą.
5በአፋቸውም ውሸት አልተገኘም፤ ነውር የለባቸውም።
6Ir aš pamačiau kitą angelą, lekiantį dangaus viduriu, turintį amžinąją Evangeliją, kad ją paskelbtų žemės gyventojams, kiekvienai giminei, genčiai, kalbai ir tautai.
6በምድርም ለሚኖሩ ለሕዝብም ለነገድም ለቋንቋም ለወገንም ሁሉ ይሰብክ ዘንድ የዘላለም ወንጌል ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ መካከል ሲበር አየሁ፤
7Jis šaukė galingu balsu: “Bijokite Dievo ir atiduokite Jam šlovę, nes atėjo Jo teismo valanda; šlovinkite Tą, kuris sutvėrė dangų ir žemę, jūrą ir vandens šaltinius!”
7በታላቅ ድምፅም። የፍርዱ ሰዓት ደርሶአልና እግዚአብሔርን ፍሩ ክብርንም ስጡት፤ ሰማይንና ምድርንም ባሕርንም የውኃንም ምንጮች ለሠራው ስገዱለት አለ።
8Paskui jį skrido antras angelas, kuris šaukė: “Krito, krito Babelė, didis miestas, kuris savo paleistuvystės įniršio vynu nugirdė visas tautas!”
8ሌላም ሁለተኛ መልአክ። አሕዛብን ሁሉ የዝሙትዋን ቍጣ ወይን ጠጅ ያጠጣች ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች እያለ ተከተለው።
9Ir trečias angelas lydėjo juos, šaukdamas skardžiu balsu: “Kas garbina žvėrį ir jo atvaizdą bei priima ant savo kaktos ar rankos ženklą,
9ሦስተኛም መልአክ ተከተላቸው፥ በታላቅ ድምፅ እንዲህ እያለ። ለአውሬውና ለምስሉ የሚሰግድ በግምባሩም ወይም በእጁ ምልክቱን የሚቀበል ማንም ቢኖር፥
10tas gers Dievo įniršio vyno, įpilto ir neatmiešto Jo rūstybės taurėje, ir bus kankinamas ugnimi ir siera šventųjų angelų ir Avinėlio akivaizdoje.
10እርሱ ደግሞ በቍጣው ጽዋ ሳይቀላቅል ከተዘጋጀው ከእግዚአብሔር ቍጣ ወይን ጠጅ ይጠጣል፥ በቅዱሳንም መላእክትና በበጉ ፊት በእሳትና በዲን ይሳቀያል።
11Jų kankinimo dūmai kils per amžių amžius, ir jie neturės atilsio nei dieną, nei naktį­tie, kurie garbina žvėrį bei jo atvaizdą ir ima jo vardo ženklą”.
11የሥቃያቸውም ጢስ ለዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ይወጣል፥ ለአውሬውና ለምስሉም የሚሰግዱ የስሙንም ምልክት የሚቀበል ሁሉ ቀንና ሌሊት ዕረፍት የላቸውም።
12Čia pasirodo šventųjų ištvermė, kurie laikosi Dievo įsakymų ir Jėzaus tikėjimo.
12የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁት ኢየሱስንም በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው በዚህ ነው።
13Ir aš išgirdau iš dangaus balsą, kuris man sakė: “Rašyk: ‘Nuo šiol palaiminti mirusieji, kurie miršta Viešpatyje. Taip,­sako Dvasia,­ kad atilsėtų nuo savo vargų; ir jų darbai seka juos’ ”.
13ከሰማይም። ከእንግዲህ ወዲህ በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብፁዓን ናቸው። መንፈስ። አዎን፥ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ፥ ሥራቸውም ይከተላቸዋል ይላል ብለህ ጻፍ የሚል ድምፅ ሰማሁ።
14Ir aš regėjau: štai baltas debesis, o ant debesies sėdėjo panašus į Žmogaus Sūnų. Ant galvos Jis turėjo aukso vainiką, o rankoje­aštrų pjautuvą.
14አየሁም፥ እነሆም ነጭ ደመና፥ በደመናውም ላይ የሰውን ልጅ የሚመስል ተቀምጦአል፥ በራሱም ላይ የወርቅ አክሊል በእጁም ስለታም ማጭድ ነበረው።
15Iš šventyklos išėjo dar vienas angelas, kuris šaukė galingu balsu sėdinčiajam ant debesies: “Paleisk darban savo pjautuvą ir pjauk; atėjo Tau valanda pjauti, nes žemės derlius prinoko”.
15ሌላ መልአክም ከመቅደሱ ወጥቶ በደመናው ላይ ለተቀመጠው። የማጨድ ሰዓት ስለ ደረሰ ማጭድህን ስደድና እጨድ፥ የምድሪቱ መከር ጠውልጓልና ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ።
16Tuomet sėdintysis ant debesies nusviedė savo pjautuvą žemėn, ir žemės derlius buvo nupjautas.
16በደመናውም ላይ የተቀመጠው ማጭዱን ወደ ምድር ጣለው ምድርም ታጨደች።
17Dar kitas angelas išėjo iš dangaus šventyklos, taip pat turintis aštrų pjautuvą.
17ሌላ መልአክም በሰማይ ካለው መቅደስ ወጣ፥ እርሱም ደግሞ ስለታም ማጭድ ነበረው።
18Ir dar vienas angelas išėjo nuo aukuro, turintis valdžią ugniai. Jis stipriu balsu sušuko turinčiajam aštrų pjautuvą: “Paleisk darban savo aštrųjį pjautuvą ir nurink žemės vynmedžio kekes, nes uogos jau prinoko”.
18በእሳትም ላይ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከመሠዊያው ወጥቶ ስለታም ማጭድ ያለውን። ዘለላዎቹ ፈጽመው በስለዋልና ስለታሙን ማጭድህን ስደድና በምድር ያለውን የወይን ዛፍ ዘለላዎች ቍረጥ ብሎ በታላቅ ድምፅ ጠራ።
19Tada angelas numetė savo pjautuvą žemėn, nuskynė žemės vynmedį ir supylė vynuoges į didįjį Dievo rūstybės spaustuvą.
19መልአኩም ማጭዱን ወደ ምድር ጣለው፥ በምድርም ካለው ከወይን ዛፍ ቈርጦ ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር ቍጣ መጥመቂያ ጣለ።
20Spaustuvas buvo minamas už miesto, ir išsiveržė iš spaustuvo kraujas, pakildamas arkliams iki žąslų tūkstančio šešių šimtų stadijų atstumu.
20የወይኑም መጥመቂያ ከከተማ ውጭ ተረገጠ፥ እስከ ፈረሶች ልጓምም የሚደርስ ደም ርቀቱ ሺህ ስድስት መቶ ምዕራፍ ሆኖ ከመጥመቂያው ወጣ።