1Ir aš pamačiau danguje dar vieną didį ir įspūdingą ženklą: septynis angelus, turinčius septynias paskutines negandas, nes jomis išsibaigia Dievo rūstybė.
1ሌላም ታላቅና ድንቅ ምልክት በሰማይ አየሁ፤ የእግዚአብሔር ቍጣ በእነርሱ ስለሚፈጸም ኋለኛዎቹን ሰባት መቅሠፍቶች የያዙ ሰባት መላእክት ታዩ።
2Aš išvydau tarsi stiklo jūrą, sumaišytą su ugnimi, ir nugalėjusiuosius žvėrį, jo atvaizdą, jo ženklą ir jo vardo skaičių, stovinčius su Dievo arfomis ant stiklo jūros.
2በእሳትም የተቀላቀለውን የብርጭቆ ባሕር የሚመስለውን አየሁ፥ በአውሬውና በምስሉም በስሙም ቍጥር ላይ ድል ነሥተው የነበሩት የእግዚአብሔርን በገና ይዘው በብርጭቆ ባሕር ላይ ሲቆሙ አየሁ።
3Jie giedojo Dievo tarno Mozės giesmę ir Avinėlio giesmę: “Didingi ir nuostabūs Tavo darbai, Viešpatie, visagali Dieve! Teisingi ir tikri Tavo keliai, šventųjų Karaliau!
3ሁሉን የምትገዛ ጌታ አምላክ ሆይ፥ ሥራህ ታላቅና ድንቅ ነው፤ የአሕዛብ ንጉሥ ሆይ፥ መንገድህ ጻድቅና እውነተኛ ነው፤ ጌታ ሆይ፥ የማይፈራህና ስምህን የማያከብር ማን ነው? አንተ ብቻ ቅዱስ ነህና፥ የጽድቅም ሥራህ ስለ ተገለጠ አሕዛብ ሁሉ ይመጣሉ በፊትህም ይሰግዳሉ እያሉ የእግዚአብሔርን ባሪያ የሙሴን ቅኔና የበጉን ቅኔ ይዘምራሉ።
4Kas gi nesibijotų Tavęs, Viešpatie, ir nešlovintų Tavojo vardo?! Juk Tu vienas šventas! Visos tautos ateis ir pagarbins Tave, nes apreikšti Tavo teisūs sprendimai”.
5ከዚህም በኋላ አየሁ፥ የምስክርም ድንኳን መቅደስ በሰማይ ተከፈተ፥
5Paskui aš regėjau: štai atsidarė Liudijimo palapinės šventykla danguje,
6ሰባቱንም መቅሠፍት የያዙ ሰባቱ መላእክት ከመቅደሱ ወጡ፤ ከተልባ እግርም የተሠራ ጥሩ የጌጥ ልብስ ለበሱ ደረታቸውንም በወርቅ መታጠቂያ ታጠቁ።
6ir išėjo iš šventyklos septyni angelai, turintys septynias negandas. Jie buvo apsivilkę tyra, spindinčia drobe ir persijuosę per krūtines aukso juostomis.
7ከአራቱም እንስሶች አንዱ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ የሚኖር የእግዚአሔር ቍጣ የሞላባቸውን ሰባት የወርቅ ጽዋዎች ለሰባቱ መላእክት ሰጣቸው።
7Viena iš keturių būtybių padavė septyniems angelams septynis aukso dubenis, pilnus Gyvenančiojo per amžių amžius Dievo rūstybės.
8ከእግዚአብሔርም ክብርና ከኃይሉ ጢስ በመቅደሱ ሞላበት፥ የሰባቱ መላእክት ሰባቱ መቅሰፍት እስኪፈጸሙ ድረስ አንድ እንኳ ወደ መቅደሱ ይገባ ዘንድ አልቻለም።
8Šventykla prisipildė dūmų nuo Dievo šlovės ir galybės, ir niekas negalėjo įeiti šventyklon, kol nesibaigs septynių angelų septynios negandos.