Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

16

1Ir išgirdau iš šventyklos galingą balsą, sakantį septyniems angelams: “Eikite ir išpilkite septynis Dievo rūstybės dubenis žemėn!”
1ለሰባቱም መላእክት። ሄዳችሁ የእግዚአብሔርን ቁጣ ጽዋዎች በምድር ውስጥ አፍስሱ የሚል ታላቅ ድምፅ ከመቅደሱ ሰማሁ።
2Ir nuėjo pirmasis, ir išliejo savo dubenį žemėn. Ir apniko piktos ir skaudžios votys žmones, turinčius žvėries ženklą ir garbinančius jo atvaizdą.
2ፊተኛውም ሄዶ ጽዋውን በምድር ውስጥ አፈሰሰ፤ የአውሬውም ምልክት ባለባቸው ለምስሉም በሚሰግዱ ሰዎች ክፉኛ የሚነዘንዝ ቍስል ሆነባቸው።
3Antrasis angelas išpylė savo dubenį jūron; ji tapo lyg numirėlio kraujas, ir visi gyviai jūroje išgaišo.
3ሁለተኛውም ጽዋውን በባሕር ውስጥ አፈሰሰ፤ እንደ ሞተም ሰው ደም ሆነ፥ በባሕርም ከሚኖሩት ሕይወት ያለበት ነፍስ ሁሉ ሞተ።
4Trečiasis angelas išliejo savo dubenį į upes ir vandens šaltinius, ir jie pavirto krauju.
4ሦስተኛውም ጽዋውን በወንዞችና በውኃ ምንጮች ውስጥ አፈሰሰ፤ እነርሱም ደም ሆኑ።
5Ir išgirdau vandenų angelą sakant: “Teisus Tu, o Viešpatie, kuris esi ir kuris buvai, šventas, kad taip teisi.
5የውኃውም መልአክ። ያለህና የነበርህ ጌታ ሆይ፥ ቅዱስ ሆይ፥ እንዲህ ስለፈረድህ ጻድቅ ነህ፤
6Nes jie praliejo šventųjų ir pranašų kraują, todėl duodi jiems gerti kraują. Taip! Jie to verti!”
6የቅዱሳንና የነቢያትን ደም ስላፈሰሱ ደምን ደግሞ አጠጥተሃቸዋል፥ የሚገባቸው ነውና ብሎ ሲናገር ሰማሁ።
7Aš dar išgirdau kitą, nuo aukuro sakant: “Taip, visagali Viešpatie Dieve, tavo nuosprendžiai tikri ir teisingi!”
7ከመሰዊያውም። አዎን፥ ሁሉን የምትገዛ ጌታ አምላክ ሆይ፥ ፍርዶችህ እውነትና ጽድቅ ናቸው ብሎ ሲናገር ሰማሁ።
8Ketvirtasis angelas išpylė savo dubenį saulėn, ir jai buvo duota svilinti žmones ugnimi.
8አራተኛውም ጽዋውን በፀሐይ ላይ አፈሰሰ፤ ሰዎችንም በእሳት ልታቃጥል ተሰጣት።
9Žmones degino baisi kaitra, o jie keikė vardą Dievo, kuris turi valdžią šitoms negandoms. Ir jie neatgailavo, kad atiduotų Jam šlovę.
9ሰዎችም በታላቅ ትኵሳት ተቃጠሉ፥ በነዚህም መቅሠፍቶች ላይ ሥልጣን ያለውን የእግዚአብሔርን ስም ተሳደቡ፥ ክብርንም እንዲሰጡት ንስሐ አልገቡም።
10Penktasis angelas išpylė savo dubenį ant žvėries sosto, ir jo karalystė paskendo tamsoje, o žmonės krimto savo liežuvius iš skausmo.
10አምስተኛውም ጽዋውን በአውሬው ዙፋን ላይ አፈሰሰ፤ መንግሥቱም ጨለማ ሆነች ከስቃይም የተነሳ መላሶቻቸውን ያኝኩ ነበር፥
11Jie piktžodžiavo dangaus Dievui dėl savo skausmų ir vočių, bet neatgailavo dėl savo darbų.
11ከስቃያቸውና ከቍስላቸውም የተነሳ የሰማይን አምላክ ተሳደቡ፥ ከስራቸውም ንስሐ አልገቡም።
12Šeštasis angelas išliejo savo dubenį į didžiąją Eufrato upę, ir jos vanduo išdžiūvo, kad pasidarytų kelias karaliams iš rytų.
12ስድስተኛውም ጽዋውን በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፤ ከፀሐይም መውጫ ለሚመጡ ነገሥታት መንገድ እንዲሰናዳላቸው ውኃው ደረቀ።
13Tada pamačiau iš slibino nasrų, iš žvėries snukio ir iš netikrojo pranašo burnos išeinant tris netyrąsias dvasias, tartum varles.
13ከዘንዶውም አፍና ከአውሬው አፍ ከሐሰተኛውም ነቢይ አፍ ጓጕንቸሮች የሚመስሉ ሦስት ርኵሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ፤
14O tai yra demonų dvasios, darančios ženklus; jos išeina pas žemės ir viso pasaulio karalius, kad juos suburtų didžiosios visagalio Dievo dienos kovai.
14ምልክት እያደረጉ የአጋንንት መናፍስት ናቸውና፥ በታላቁም ሁሉን በሚገዛ በእግዚአብሔር ቀን ወደ ሚሆነው ጦር እንዲያስከትቱአቸው ወደ ዓለም ሁሉ ነገሥታት ይወጣሉ።
15“Štai Aš ateinu kaip vagis. Palaimintas, kas budi ir saugo savo drabužius, kad netektų vaikščioti nuogam ir jie nematytų jo gėdos!”
15እነሆ፥ እንደ ሌባ ሆኜ እመጣለሁ፤ ራቁቱን እንዳይሄድ እፍረቱንም እንዳያዩ ነቅቶ ልብሱን የሚጠብቅ ብፁዕ ነው።
16Ir jis subūrė juos į vietovę, kuri hebrajiškai vadinasi Harmagedonas.
16በዕብራይስጥም አርማጌዶን ወደሚባል ስፍራ እስከተቱአቸው።
17Septintasis angelas išpylė savo dubenį į orą, ir nuskambėjo iš šventyklos, nuo sosto, galingas balsas: “Įvyko!”
17ሰባተኛውም ጽዋውን በአየር ውስጥ አፈሰሰ፤ ከመቅደሱም ውስጥ። ተፈጽሞአል የሚል ታላቅ ድምጽ ከዙፋኑ ወጣ።
18Ir radosi žaibai, griaustiniai, garsai, ir kilo didžiulis žemės drebėjimas, kokio nebuvo, kiek žmogus gyvena žemėje,­toks smarkus, toks baisus žemės drebėjimas!
18መብረቅና ድምጽም ነጎድጓድም ሆኑ፥ ትልቅም የምድር መናወጥ ሆነ፤ ሰው በምድር ከተፈጠረ ጀምሮ እንዲህ ያለ ታላቅ መናውጥ ከቶ አልነበረም፤ ከሁሉ በለጠ።
19Didysis miestas suskilo į tris dalis, ir tautų miestai sugriuvo. Ir Dievas atsiminė didžiąją Babelę, kad jai duotų savo rūstybės ir įniršio vyno taurę.
19ታላቂቱም ከተማ በሦስት ተከፋፈለች፥ የአሕዛብም ከተማዎች ወደቁ። ታላቂቱም ባቢሎን የብርቱ ቍጣው ወይን ጠጅ የሞላበትን ጽዋ እንዲሰጣት በእግዚአብሔር ፊት ታሰበች።
20Ir pabėgo visos salos, ir nebeliko kalnų.
20ደሴቶችም ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም።
21Ledo gabalai, talento svorio, krito iš dangaus ant žmonių. Žmonės keikė Dievą dėl ledų negandos, nes siaubinga buvo ši neganda.
21በሚዛንም አንድ ታላንት*ፍ1* የሚያህል ታላቅ በረዶ በሰዎች ላይ ከሰማይ ወረደባቸው፤ ሰዎቹም ከበረዶው መቅሰፍት የተነሳ እግዚአብሔርን ተሳደቡ፥ መቅሰፍቱ እጅግ ታላቅ ነውና።