Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

17

1Tuomet atėjo vienas iš septynių angelų, turėjusių septynis dubenis, ir prakalbino mane, sakydamas: “Eikš, aš parodysiu tau teismą didžiosios paleistuvės, sėdinčios ant daugybės vandenų.
1ሰባቱንም ጽዋዎች ከያዙ ከሰባቱ መላእክት አንዱ መጥቶ። ና በብዙም ውኃዎች ላይ የተቀመጠችውን የታላቂቱን ጋለሞታ ፍርድ አሳይሃለሁ፤
2Su ja ištvirkavo žemės karaliai, ir jos ištvirkavimo vynu pasigėrė žemės gyventojai”.
2የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ በምድርም የሚኖሩ ከዝሙትዋ ወይን ጠጅ ሰከሩ ብሎ ተናገረኝ።
3Ir jis Dvasia nunešė mane į dykumą. Ir aš išvydau moterį, sėdinčią ant skaisčiai raudono žvėries, pilno piktžodžiavimo vardų, turinčio septynias galvas ir dešimt ragų.
3በመንፈስም ወደ በረሀ ወሰደኝ፤ የስድብም ስሞች በሞሉበት፥ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ባሉበት በቀይ አውሬ ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ አየሁ።
4Moteris buvo apsivilkusi purpuru ir škarlatu, išsipuošusi auksu, brangakmeniais ir perlais. Ji laikė rankoje aukso taurę, pilną savo ištvirkavimo šlykštybių ir nešvarumų.
4ሴቲቱም በቀይና በሐምራዊ ልብስ ተጐናጽፋ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች በዕንቈችም ተሸልማ ነበር፥ በእጅዋም የሚያስጸይፍ ነገር የዝሙትዋም ርኵሰት የሞላባትን የወርቅ ጽዋ ያዘች፤
5Ant jos kaktos buvo užrašytas vardas: “Paslaptis, didžioji Babelė, ištvirkėlių ir žemės šlykštybių motina”.
5በግምባርዋም ምስጢር የሆነ ስም። ታላቂቱ ባቢሎን፥ የጋለሞታዎችና የምድር ርኵሰት እናት ተብሎ ተጻፈ።
6Mačiau tą moterį, girtą nuo šventųjų kraujo ir nuo Jėzaus liudytojų kraujo. Ją matydamas, aš stebėte stebėjausi.
6ሴቲቱም በቅዱሳን ደምና በኢየሱስ ምስክሮች ደም ሰክራ አየኋት። ባየኋትም ጊዜ እጅግ ታላቅ ድንቅ አደነቅሁ።
7O angelas man tarė: “Ko stebiesi? Aš tau pasakysiu paslaptį moters ir ją nešančio žvėries, kuris turi septynias galvas ir dešimt ragų”.
7መልአኩም አለኝ። የምትደነቅ ስለ ምንድር ነው? የሴቲቱን ምስጢርና የሚሸከማትን፥ ሰባት ራሶችና አስር ቀንዶች ያሉትን የአውሬውን ምስጢር እኔ እነግርሃለሁ።
8“Žvėris, kurį regėjai, buvo, bet jo nebėra; jis ruošiasi išlipti iš bedugnės, tačiau eina į pražūtį. Žemės gyventojai, kurių vardai nėra įrašyti gyvenimo knygoje nuo pasaulio sutvėrimo, stebėsis, žiūrėdami į žvėrį, kad jis buvo ir jo nebėra, ir jis vėl pasirodys.
8ያየኸው አውሬ አስቀድሞ ነበረ፥ አሁንም የለም፥ ከጥልቁም ይወጣ ዘንድ አለው፥ ወደ ጥፋትም ይሄዳል፤ ስሞቻቸውም ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ በሕይወት መጽሐፍ ያልተጻፉ በምድር የሚኖሩ አውሬው አስቀድሞ እንደነበረ አሁንም እንደሌለ፥ ነገር ግን እንዳለ ሲያዩ ያደንቃሉ።
9Čia reikia proto, turinčio išmintį! Septynios galvos reiškia septynis kalnus, ant kurių sėdi moteris.
9ጥበብ ያለው አእምሮ በዚህ ነው። ሰባቱ ራሶች ሴቲቱ የተቀመጠችባቸው ሰባት ተራራዎች ናቸው፥
10Taip pat yra septyni karaliai; penki žlugo, vienas tebėra, o vienas dar neatėjo; kai jis ateis, turės trumpam pasilikti.
10ሰባት ነገሥታት ደግሞ ናቸው፤ አምስቱ ወድቀዋል አንዱም አለ፥ የቀረውም ገና አልመጣም፤ ሲመጣም፥ ጥቂት ጊዜ ሊቆይ ይገባዋል።
11O žvėris, kuris buvo ir kurio nebėra,­tai aštuntasis, bet vienas iš septynių, ir jis eina į pražūtį.
11የነበረውና የሌለውም አውሬ ራሱ ደግሞ ስምንተኛው ነው ከሰባቱም አንዱ ነው፥ ወደ ጥፋትም ይሄዳል።
12Tie dešimt ragų, kuriuos matei, yra dešimt karalių, kurie dar negavo karalystės, bet jie gaus valdžią kaip karaliai vienai valandai kartu su žvėrimi.
12ያየሃቸውም አስሩ ቀንዶች ገና መንግሥትን ያልተቀበሉ አስር ነገሥታት ናቸው፥ ዳሩ ግን ከአውሬው ጋር ለአንድ ሰዓት እንደ ነገሥታት ሥልጣንን ይቀበላሉ።
13Jie turi vieną tikslą ir savo jėgą bei valdžią atiduos žvėriui.
13እነዚህ አንድ አሳብ አላቸው፥ ኃይላቸውንና ሥልጣናቸውንም ለአውሬው ይሰጣሉ።
14Jie kovos su Avinėliu, bet Avinėlis juos nugalės, nes Jis yra viešpačių Viešpats ir karalių Karalius, ir su juo visi pašauktieji, išrinktieji ir ištikimieji”.
14እነዚህ በጉን ይወጋሉ፤ በጉም የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ ስለ ሆነ እነርሱን ድል ይነሣል፥ ከእርሱም ጋር ያሉ የተጠሩና የተመረጡ የታመኑም ደግሞ ድል ይነሣሉ።
15Angelas toliau man sako: “Vandenys, kuriuos regėjai, kur sėdi paleistuvė, yra žmonės, minios, tautos ir kalbos.
15አለኝም። ጋለሞታይቱ የተቀመጠችባቸው ያየሃቸው ውኃዎች፥ ወገኖችና ብዙ ሰዎች አሕዛብም ቋንቋዎችም ናቸው።
16Tie dešimt ragų, kuriuos matei ant žvėries­jie ims nekęsti paleistuvės, apiplėš ją ir paliks ją nuogą, ės jos kūną ir ją pačią sudegins ugnyje.
16ያየኃቸውም አስር ቀንዶችና አውሬው ጋለሞታይቱን ይጣላሉ፤ ባዶዋንና ራቁትዋንም ያደርጓታል፥ ሥጋዋንም ይበላሉ፥ በእሳትም ያቃጥሉአታል።
17Nes Dievas įkvėpė jų širdis vykdyti Jo tikslą, vykdyti vieną tikslą,­kad jie atiduotų savo karalystę žvėriui, kol išsipildys Dievo žodžiai.
17እግዚአብሔር አሳቡን እንዲያደርጉ አንድንም አሳብ እንዲያደርጉ የእግዚአብሔርም ቃል እስኪፈጸም ድረስ መንግሥታቸውን ለአውሬው እንዲሰጡ በልባቸው አግብቶአልና።
18Ta moteris, kurią regėjai, yra didysis miestas, valdantis žemės karalius”.
18ያየሃትም ሴት በምድር ነገሥታት ላይ የምትነግሥ ታላቂቱ ከተማ ናት።