Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

18

1Paskui aš išvydau kitą angelą, nužengiantį iš dangaus ir turintį didžią valdžią. Žemė nušvito nuo jo šlovės.
1ከዚህ በኋላ ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች።
2O jis šaukė galingai, stipriu balsu: “Krito, krito didžioji Babelė! Ji pavirto demonų buveine, visų netyrųjų dvasių pastoge, visų nešvarių ir nekenčiamų paukščių narvu.
2በብርቱም ድምፅ። ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤
3Nuo jos ištvirkimo įniršio vyno buvo girtos visos tautos; žemės karaliai su ja ištvirkavo, o žemės pirkliai pralobo iš jos nežabotos prabangos”.
3አሕዛብ ሁሉ ከዝሙትዋ ቍጣ ወይን ጠጅ የተነሳ ወድቀዋልና፥ የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነትዋ ኃይል የተነሳ ባለ ጠጋዎች ሆኑ ብሎ ጮኸ።
4Ir aš išgirdau iš dangaus kitą balsą, skelbiantį: “Išeikite iš jos, mano žmonės, kad nedalyvautumėte jos nuodėmėse ir nepatirtumėte jos negandų!
4ከሰማይም ሌላ ድምፅ ሰማሁ እንዲህ ሲል። ሕዝቤ ሆይ፥ በኃጢአትዋ እንዳትተባበሩ ከመቅሠፍትዋም እንዳትቀበሉ ከእርስዋ ዘንድ ውጡ፤
5Nes jos nuodėmės pasiekė dangų, ir Dievas prisiminė jos piktadarystes.
5ኃጢአትዋ እስከ ሰማይ ድረስ ደርሶአልና፥ እግዚአብሔርም ዓመፃዋን አሰበ።
6Atmokėkite jai, kaip ji jums atlygino, ir atiduokite dvigubai pagal jos darbus. Dvigubai sumaišykite taurę, kurią ji jums maišė.
6እርስዋ እንደ ሰጠች መጠን ብድራት መልሱላት፥ እንደ ሥራዋም ሁለት እጥፍ ደርቡባት፤ በቀላቀለችው ጽዋ ሁለት እጥፍ አድርጋችሁ ቀላቅሉባት፤
7Kiek ji puikavo ir lėbavo, tiek jai paruoškite kentėjimų ir nuliūdimo, nes ji savo širdyje kalba: ‘Aš sėdžiu kaip karalienė, nesu našlė ir liūdesio nematysiu’.
7ራስዋን እንደ አከበረችና እንደ ተቀማጠለች ልክ ሥቃይና ኀዘን ስጡአት። በልብዋ። ንግሥት ሆኜ እቀመጣለሁ ባልቴትም አልሆንም ኀዘንም ከቶ አላይም ስላለች፥
8Todėl vieną dieną ją apniks negandos: mirtis, gedulas, badas, ir ji bus sudeginta ugnyje, nes galingas yra Viešpats Dievas, kuris nuteisė ją.
8ስለዚህ በአንድ ቀን ሞትና ኀዘን ራብም የሆኑ መቅሰፍቶችዋ ይመጣሉ፥ በእሳትም ትቃጠላለች፤ የሚፈርድባት እግዚአብሔር ብርቱ ነውና።
9Jos verks ir raudos žemės karaliai, kurie su ja ištvirkavo bei lėbavo, kai pamatys jos gaisro dūmus.
9ከእርስዋም ጋር የሴሰኑና የተቀማጠሉ የምድር ነገሥታት የመቃጠልዋን ጢስ ሲያዩ ስለ እርስዋ ዋይ ዋይ እያሉ ያለቅሳሉ፤
10Jie stovės iš tolo ir, jos kankinimų išgąsdinti, sakys: ‘Vargas, vargas, didysis mieste! Babele, galingasis mieste, per vieną valandą įvyko tavo teismas!’
10ሥቃይዋንም ከመፍራት የተነሣ በሩቅ ቆመው። አንቺ ታላቂቱ ከተማ፥ ብርቱይቱ ከተማ ባቢሎን፥ ወዮልሽ፥ ወዮልሽ፥ በአንድ ሰዓት ፍርድሽ ደርሶአልና እያሉ ይናገራሉ።
11Žemės pirkliai verks ir gedės jos, nes niekas jau nebepirks jų atplukdytų prekių:
11የመርከባቸውንም ጭነት ከእንግዲህ ወዲህ የሚገዛ የለምና የምድር ነጋዴዎች ያለቅሱላታል ያዝኑላትማል፤
12aukso, sidabro, brangakmenių, perlų, švelnios drobės, purpuro, šilko, škarlato, jokios kvapios medienos, jokių dramblio kaulo dirbinių, jokių brangmedžio rakandų, nei vario, geležies, marmuro,
12ጭነትም ወርቅና ብር የከበረም ድንጋይ ዕንቁም፥ ቀጭንም ተልባ እግር ቀይም ሐርም ሐምራዊም ልብስ የሚሸትም እንጨት ሁሉ፥ ከዝሆን ጥርስም የተሰራ ዕቃ ሁሉ፥ እጅግም ከከበረ እንጨት ከናስም ከብረትም ከዕብነ በረድም የተሰራ ዕቃ ሁሉ፥
13cinamono, kvapių augalų, miros, smilkalų, vyno, aliejaus, smulkių miltų, kviečių, galvijų, avių, arklių, vežimų, žmonių kūnų ir sielų.
13ቀረፋም ቅመምም የሚቃጠልም ሽቱ ቅባትም ዕጣንም የወይን ጠጅም ዘይትም የተሰለቀ ዱቄትም ስንዴም ከብትም በግም ፈረስም ሰረገላም ባሪያዎችም የሰዎችም ነፍሳት ነው።
14Vaisiai, kurių taip geidė tavo siela, nutolo nuo tavęs; visas puošnumas ir spindesys tau pražuvo, ir niekad jų neberasi.
14ነፍስሽም የጎመጀችው ፍሬ ከአንቺ ዘንድ አልፎአል፥ የሚቀማጠልና የሚያጌጥም ነገር ሁሉ ጠፍቶብሻል፥ ሰዎችም ከእንግዲህ ወዲህ ከቶ አያገኙአቸውም።
15Tų daiktų pirkliai, iš jos pralobę, stovės iš tolo, išsigandę jos kankinimų, verks, gedės
15እነዚህን የነገዱ በእርስዋም ባለ ጠጋዎች የሆኑት እያለቀሱና እያዘኑ። በቀጭን ተልባ እግርና በቀይ ሐምራዊም ልብስ ለተጐናጸፈች በወርቅና በከበረ ድንጋይም በዕንቁም ለተሸለመች ለታላቂቱ ከተማ ወዮላት፥ ወዮላት፥ ይህን የሚያህል ታላቅ ባለ ጠግነት በአንድ ሰዓት ጠፍቶአልና እያሉ ስቃይዋን ከመፍራት የተነሣ በሩቅ ይቆማሉ። የመርከብም መሪ ሁሉ በመርከብም ወደ ማናቸውም ስፍራ የሚሄድ ሁሉ መርከበኞችም ከባሕርም የሚጠቀሙ ሁሉ በሩቅ ቆሙ፥
16ir sakys: ‘Vargas, vargas didžiajam miestui, vilkėjusiam ploniausia drobe, purpuru, škarlatu, išsipuošusiam auksu, brangakmeniais ir perlais.
18የመቃጠልዋንም ጢስ ባዩ ጊዜ። ታላቂቱን ከተማ የምትመስላት ምን ከተማ ነበረች? እያሉ ጮኹ።
17Per vieną valandą niekais virto šitokie turtai!’ Visi laivų vairininkai, visi pakrančių laivininkai, visi jūreiviai ir visi, kurie jūroje darbuojasi, iš tolo sustoję
19በራሳቸውም ላይ ትቢያ ነስንሰው እያለቀሱና እያዘኑ። በባሕር መርከቦች ያሉአቸውን ሁሉ ከባለ ጠግነትዋ የተነሣ ባለ ጠጋዎች ላደረገች ለታላቂቱ ከተማ ወዮላት፥ ወዮላት፥ በአንድ ሰዓት ጠፍታለችና እያሉ ጮኹ።
18ir, stebėdami jos gaisro dūmus, šaukė: ‘Kas galėtų lygintis su didžiuoju miestu?!’
20ሰማይ ሆይ፥ ቅዱሳን ሐዋርያት ነቢያትም ሆይ፥ በእርስዋ ላይ ደስ ይበላችሁ፥ እግዚአብሔር ፈርዶላችኋልና።
19Jie bėrė žemes ant galvų, šaukė, verkė ir aimanavo: ‘Vargas, vargas didžiajam miestui, iš kurio prabangos pralobo, kurie jūroje turėjo laivų. Per vieną valandą jis virto dykyne!’
21አንድም ብርቱ መልአክ ትልቅን ወፍጮ የሚመስልን ድንጋይ አንስቶ ወደ ባሕር ወረወረው እንዲህ ሲል። ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን እንዲህ ተገፍታ ትወድቃለች ከእንግዲህም ወዲህ ከቶ አትገኝም።
20Džiūgauk dėl jo, dangau, ir jūs, šventieji, ir apaštalai, ir pranašai, nes dėl jūsų Dievas nubaudė jį teismu!”
22በገና የሚመቱና የሚዘምሩም ድምፅ እንቢልታንና መለከትንም የሚነፉ ድምፅ ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይሰማም፥ የእጅ ጥበብም ሁሉ አንድ ብልሃተኛ እንኳ ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይገኝም፥ የወፍጮ ድምጽም ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይሰማም፥
21Tuomet vienas galingas angelas iškėlė akmenį, tarsi didelį girnakmenį, ir sviedė jį į jūrą, sakydamas: “Tokiu smarkumu bus nublokštas didysis Babelės miestas, ir jo nebebus galima rasti.
23የመብራትም ብርሃን ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይበራም፥ የሙሽራና የሙሽራይቱም ድምጽ ከእንግዲህ ወዲህ በአንቺ ውስጥ ከቶ አይሰማም፤ ነጋዴዎችሽ የምድር መኳንንት ነበሩና፥ በአስማትሽም አሕዛብ ሁሉ ስተዋልና።
22Nebesigirdės daugiau tavyje arfininkų, giesmininkų, vamzdininkų, trimitininkų balsų. Niekas neberas tavyje nė vieno jokio meno kūrėjo, ir nebesigirdės tavyje malūno dūzgimo.
24በእርስዋም ውስጥ የነቢያትና የቅዱሳን ደም በምድርም የታረዱ ሁሉ ደም ተገኘባት።
23Tavyje nebešvies žiburio spindulys, niekas nebegirdės jaunikio ir nuotakos balso. Nes tavo pirkliai buvo tapę žemės didžiūnais, nes tavo burtais buvo suvedžiotos visos tautos
24ir tavyje buvo rastas pranašų ir šventųjų ir visų žemėje nužudytųjų kraujas”.