Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

2

1“Efezo bažnyčios angelui rašyk: ‘Tai sako Tas, kuris laiko savo dešinėje septynias žvaigždes, kuris vaikščioja tarp septynių aukso žibintuvų.
1በኤፌሶን ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። በቀኝ እጁ ሰባቱን ከዋክብት የያዘው በሰባቱም የወርቅ መቅረዞች መካከል የሚሄደው እንዲህ ይላል።
2Aš žinau tavo darbus, tavo triūsą ir tavo kantrybę. Žinau, kad tu negali pakęsti piktųjų ir ištyrei tuos, kurie sakosi esą apaštalai, bet tokie nėra, ir radai juos esant melagius.
2ሥራህንና ድካምህን ትዕግሥትህንም አውቃለሁ፤ ክፉዎችንም ልትታገሥ እንዳትችል፥ እንዲሁም ሳይሆኑ። ሐዋርያት ነን የሚሉቱን መርምረህ ሐሰተኞች ሆነው እንዳገኘሃቸው አውቃለሁ፤
3Tu ištvėrei, esi kantrus ir dėl mano vardo triūsei ir nepailsai.
3ታግሠህማል፥ ስለ ስሜም ብለህ ጸንተህ አልደከምህም።
4Bet Aš turiu prieš tave tai, kad palikai savo pirmąją meilę.
4ዳሩ ግን የምነቅፍብህ ነገር አለኝ የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና።
5Taigi prisimink, nuo kur nupuolei, atgailauk ir vėl imkis pirmykščių darbų, o jeigu ne,­jei neatgailausi,­greitai ateisiu ir patrauksiu iš vietos tavo žibintuvą.
5እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፤ አለዚያ እመጣብሃለሁ ንስሐም ባትገባ መቅረዝህን ከስፍራው እወስዳለሁ።
6Savo naudai tu turi, kad nekenti nikolaitų darbų, kurių ir Aš nekenčiu’.
6ነገር ግን ይህ አለህ፤ እኔ ደግሞ የምጠላውን የኒቆላውያንን ሥራ ጠልተሃልና።
7Kas turi ausis, teklauso, ką Dvasia sako bažnyčioms: ‘Nugalėtojui Aš duosiu valgyti nuo gyvybės medžio, esančio Dievo rojaus viduryje’ ”.
7መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት ዛፍ እንዲበላ እሰጠዋለሁ።
8“Smirnos bažnyčios angelui rašyk: ‘Tai sako Pirmasis ir Paskutinysis, kuris buvo miręs ir vėl grįžo į gyvenimą.
8በሰምርኔስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። ሞቶ የነበረው ሕያውም የሆነው ፊተኛውና መጨረሻው እንዲህ ይላል።
9Aš žinau tavo darbus ir priespaudą, ir tavo skurdą,­o vis dėlto tu turtingas!­ir kaip tau piktžodžiauja tie, kurie sakosi esą žydai, bet nėra tokie, o tik šėtono sinagoga.
9መከራህንና ድህነትህን አውቃለሁ፥ ነገር ግን ባለ ጠጋ ነህ፤ የሰይጣንም ማኅበር ናቸው እንጂ አይሁድ ሳይሆኑ። አይሁድ ነን የሚሉት የሚሳደቡትን ስድብ አውቃለሁ።
10Nebijok būsimųjų kentėjimų. Štai velnias įmes kai kuriuos jūsiškius į kalėjimą, kad būtumėte išbandyti. Jūsų laukia dešimties dienų priespauda. Būk ištikimas iki mirties, ir Aš tau duosiu gyvenimo vainiką’.
10ልትቀበለው ያለህን መከራ አትፍራ። እነሆ፥ እንድትፈተኑ ዲያብሎስ ከእናንተ አንዳንዶቻችሁን በወኅኒ ሊያገባችሁ አለው፥ አሥር ቀንም መከራን ትቀበላላችሁ። እስከሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ።
11Kas turi ausis, teklauso, ką Dvasia sako bažnyčioms: ‘Nugalėtojas nenukentės nuo antrosios mirties’ ”.
11መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል የነሣው በሁለተኛው ሞት አይጐዳም።
12“Pergamo bažnyčios angelui rašyk: ‘Tai sako Tas, kuris turi aštrų dviašmenį kalaviją.
12በጴርጋሞንም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። በሁለት ወገን የተሳለ ስለታም ሰይፍ ያለው እንዲህ ይላል።
13Aš žinau tavo darbus ir kur tu gyveni: ten, kur šėtono sostas. Bet tu tvirtai laikaisi mano vardo ir neišsigynei mano tikėjimo net tomis dienomis, kada pas jus,­kur gyvena šėtonas,­buvo nužudytas mano ištikimasis liudytojas Antipas.
13የሰይጣን ዙፋን ባለበት የምትኖርበትን አውቃለሁ፤ ስሜንም ትጠብቃለህ፥ ሰይጣንም በሚኖርበት፥ በእናንተ ዘንድ የተገደለው የታመነው ምስክሬ አንቲጳስ በነበረበት ዘመን እንኳ ሃይማኖቴን አልካድህም።
14Vis dėlto turiu šį tą prieš tave: tu tenai turi besilaikančių Balaamo mokslo, kuris mokė Balaką suvedžioti Izraelio sūnus, kad šie valgytų stabams aukojamas aukas ir ištvirkautų.
14ዳሩ ግን ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉና እንዲሴስኑ በእስራኤል ልጆች ፊት ማሰናከያን ሊያኖርባቸው ባላቅን ያስተማረ የበልዓምን ትምህርት የሚጠብቁ በዚያ ከአንተ ጋር ስላሉ፥ የምነቅፍብህ ጥቂት ነገር አለኝ።
15Ir tu taip pat turi besilaikančių nikolaitų mokslo, kurio Aš nekenčiu.
15እንዲሁ የኒቆላውያንን ትምህርት እንደ እነዚህ የሚጠብቁ ሰዎች ከአንተ ጋር ደግሞ አሉ።
16Tad atgailauk! O jeigu ne, Aš greitai ateisiu ir kovosiu su jais savo burnos kalaviju’.
16እንግዲህ ንስሐ ግባ፤ አለዚያ ፈጥኜ እመጣብሃለሁ፥ በአፌም ሰይፍ እዋጋቸዋለሁ።
17Kas turi ausis, teklauso, ką Dvasia sako bažnyčioms: ‘Nugalėtojui Aš duosiu paslėptos manos ir baltą akmenėlį, o ant akmenėlio bus įrašytas naujas vardas, kurio niekas nežino, tiktai gavėjas’ ”.
17መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል ለነሣው ከተሰወረ መና እሰጠዋለሁ፥ ነጭ ድንጋይንም እሰጠዋለሁ፥ በድንጋዩም ላይ ከተቀበለው በቀር አንድ ስንኳ የሚያውቀው የሌለ አዲስ ስም ተጽፎአል።
18“Tiatyrų bažnyčios angelui rašyk: ‘Tai sako Dievo Sūnus, kurio akys tarytum ugnies liepsna ir kurio kojos panašios į skaistvarį.
18በትያጥሮንም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። እንደ እሳት ነበልባል የሆኑ ዓይኖች ያሉት በእቶንም የነጠረ የጋለ ናስ የሚመስሉ እግሮች ያሉት የእግዚአብሔር ልጅ እንዲህ ይላል።
19Žinau tavo darbus, meilę, tikėjimą, tarnavimą, kantrybę ir kad tavo paskutinieji darbai didesni už pirmuosius.
19ሥራህንና ፍቅርህን እምነትህንም አገልግሎትህንም ትዕግሥትህንም ከፊተኛውም ሥራህ ይልቅ የኋለኛው እንዲበዛ አውቃለሁ።
20Bet Aš turiu šį tą prieš tave: tu leidi moteriškei Jezabelei, kuri sakosi esanti pranašė, mokyti bei suvedžioti mano tarnus, kad jie ištvirkautų ir valgytų stabams paaukotas aukas.
20ዳሩ ግን። ነቢይ ነኝ የምትለውን ባሪያዎቼንም እንዲሴስኑና ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉ የምታስተምረውንና የምታስተውን ያችን ሴት ኤልዛቤልን ስለምትተዋት የምነቅፍብህ ነገር አለኝ፤
21Aš jai daviau laiko atgailauti dėl ištvirkavimo, bet ji neatgailavo.
21ንስሐም እንድትገባ ጊዜ ሰጠኋት ከዝሙትዋም ንስሐ እንድትገባ አልወደደችም።
22Štai Aš ją nublokšiu į ligos patalą, o ištvirkavusius su ja­į didelį sielvartą, jeigu jie neatgailaus dėl savo darbų.
22እነሆ፥ በአልጋ ላይ እጥላታለሁ፥ ከእርስዋም ጋር የሚያመነዝሩትን ከሥራዋ ንስሐ ባይገቡ በታላቅ መከራ እጥላቸዋለሁ፤
23Jos vaikus išžudysiu, ir visos bažnyčios sužinos, kad Aš esu Tas, kuris ištiria protus ir širdis; Aš atsilyginsiu jums kiekvienam pagal jūsų darbus.
23ልጆችዋንም በሞት እገድላቸዋለሁ፤ አብያተ ክርስቲያናትም ሁሉ ኵላሊትንና ልብን የምመረምር እኔ እንደ ሆንሁ ያውቃሉ፥ ለእያንዳንዳችሁም እንደ ሥራችሁ እሰጣችኋለሁ።
24O jums ir kitiems tiatyriečiams, kurie nesilaiko ano mokslo, kurie, kaip sakosi, nėra pažinę šėtono gelmių, Aš sakau: neužkrausiu jums kitokios naštos,
24ዳሩ ግን ይህን ትምህርት ለማትይዙ ሁሉ የሰይጣንንም ጥልቅ ነገር እነርሱ እንደሚሉት ለማታውቁ ለእናንተ በትያጥሮን ለቀራችሁት እላለሁ፤ ሌላ ሸክም አልጭንባችሁም፥
25tiktai tvirtai laikykitės to, ką turite, iki ateisiu.
25ነገር ግን እስክመጣ ድረስ ያላችሁን ጠብቁ።
26Tam, kuris nugali ir iki galo laikosi mano darbų, Aš ‘duosiu valdžią tautoms:
26ድል ለነሣውና እስከ መጨረሻም ሥራዬን ለጠበቀው እኔ ደግሞ ከአባቴ እንደ ተቀበልሁ በአሕዛብ ላይ ሥልጣንን እሰጠዋለሁ፥ በብረትም በትር ይገዛቸዋል፥ እንደ ሸክላ ዕቃም ይቀጠቀጣሉ፤
27jis valdys jas geležine lazda, ir jos bus sudaužytos tarsi moliniai indai’,­kaip ir Aš esu gavęs valdžią iš savo Tėvo;­
28የንጋትንም ኮከብ እሰጠዋለሁ።
28ir jam duosiu aušrinę žvaigždę’.
29መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
29Kas turi ausis, teklauso, ką Dvasia sako bažnyčioms!”