1“Sardų bažnyčios angelui rašyk: ‘Tai sako Tas, kuris turi septynias Dievo Dvasias ir septynias žvaigždes. Aš žinau tavo darbus: tave vadina gyvu, o tu esi miręs.
1በሰርዴስም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስትና ሰባቱ ከዋክብት ያሉት እንዲህ ይላል። ሥራህን አውቃለሁ ሕያው እንደ መሆንህ ስም አለህ ሞተህማል።
2Budėk ir stiprink, kas dar yra ir merdi! Aš neradau tavo darbų, kurie būtų pabaigti Dievo akivaizdoje.
2ሥራህን በአምላኬ ፊት ፍጹም ሆኖ አላገኘሁትምና የነቃህ ሁን፥ ሊሞቱም ያላቸውን የቀሩትን ነገሮች አጽና።
3Todėl prisimink, kaip priėmei ir išgirdai; laikykis to ir atgailauk! Jeigu nebudėsi, ateisiu kaip vagis, ir nežinosi, kurią valandą tave užklupsiu.
3እንግዲህ እንዴት እንደ ተቀበልህና እንደ ሰማህ አስብ፥ ጠብቀውም ንስሐም ግባ። እንግዲያስ ባትነቃ እንደ ሌባ እመጣብሃለሁ በማናቸውም ሰዓት እንድመጣብህ ከቶ አታውቅም።
4Vis dėlto tu Sarduose turi keletą vardų, kurie nesutepė savo drabužių. Jie vaikščios su manimi, apsirengę baltai, nes jie to verti.
4ነገር ግን ልብሳቸውን ያላረከሱ በሰርዴስ ጥቂት ሰዎች ከአንተ ጋር አሉ፥ የተገባቸውም ስለ ሆኑ ነጭ ልብስ ለብሰው ከእኔ ጋር ይሄዳሉ።
5Nugalėtojas bus aprengtas baltais drabužiais, ir jo vardo neištrinsiu iš gyvenimo knygos. Aš išpažinsiu jo vardą savo Tėvo ir Jo angelų akivaizdoje’.
5ድል የነሣው እንዲሁ በነጭ ልብስ ይጐናጸፋል፥ ስሙንም ከሕይወት መጽሐፍ አልደመስስም፥ በአባቴና በመላእክቱም ፊት ለስሙ እመሰክርለታለሁ።
6Kas turi ausis, teklauso, ką Dvasia sako bažnyčioms”.
6መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
7“Filadelfijos bažnyčios angelui rašyk: ‘Tai kalba Šventasis, Tikrasis, turintis Dovydo raktą,Tas, kuris atidaro, ir niekas negali uždaryti, uždaro, ir niekas negali atidaryti.
7በፊልድልፍያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። የዳዊት መክፈቻ ያለው፤ የሚከፍት፥ የሚዘጋም የሌለ፤ የሚዘጋ፥ የሚከፍትም የሌለ፤ ቅዱስና እውነተኛ የሆነው እርሱ እንዲህ ይላል።
8Aš žinau tavo darbus. Štai Aš atvėriau prieš tave duris, ir niekas nebegali jų uždaryti; nedaug turi jėgų, bet išsaugojai mano žodį ir neatsižadėjai mano vardo.
8ሥራህን አውቃለሁ፤ እነሆ፥ በአንተ ፊት የተከፈተ በር ሰጥቼአለሁ ማንምም ሊዘጋው አይችልም፤ ኃይልህ ምንም ትንሽ ቢሆን ቃሌን ጠብቀሃልና፥ ስሜንም አልካድህምና።
9Štai Aš tau duodu tuos iš šėtono sinagogos, kurie tvirtina, jog jie žydai, bet nėra, nes jie meluoja. Taigi padarysiu, kad jie ateitų, pultų tau po kojų ir suprastų, jog Aš pamilau tave.
9እነሆ፥ አይሁድ ሳይሆኑ። አይሁድ ነን ከሚሉ ነገር ግን ከሚዋሹ ከሰይጣን ማኅበር አንዳንዶችን እሰጥሃለሁ እነሆ፥ መጥተው በእግሮችህ ፊት ይሰግዱ ዘንድ እኔም እንደ ወደድሁህ ያውቁ ዘንድ አደርጋቸዋለሁ።
10Kadangi tu išlaikei mano kantrybės žodį, tai ir Aš tave apsaugosiu nuo išbandymo valandos, kuri ištiks visą pasaulį, kad būtų išmėginti žemės gyventojai.
10የትዕግሥቴን ቃል ስለ ጠበቅህ እኔ ደግሞ በምድር የሚኖሩትን ይፈትናቸው ዘንድ በዓለም ሁሉ ላይ ሊመጣ ካለው ከፈተናው ሰዓት እጠብቅሃለሁ።
11Štai Aš veikiai ateinu. Tvirtai laikyk, ką turi, kad niekas neatimtų tavo vainiko.
11እነሆ፥ ቶሎ ብዬ እመጣለሁ፤ ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጽንተህ ያዝ።
12Nugalėtoją Aš padarysiu ramsčiu savo Dievo šventykloje, ir jis jau nebeišeis laukan; užrašysiu ant jo savo Dievo vardą ir vardą savo Dievo miesto, naujosios Jeruzalės, nužengiančios iš dangaus nuo mano Dievo, ir savo naująjį vardą’.
12ድል የነሣው በአምላኬ መቅደስ ዓምድ እንዲሆን አደርገዋለሁ፥ ወደ ፊትም ከዚያ ከቶ አይወጣም፤ የአምላኬን ስምና የአምላኬን ከተማ ስም፥ ማለት ከሰማይ ከአምላኬ ዘንድ የምትወርደውን አዲሲቱን ኢየሩሳሌምን፥ አዲሱንም ስሜን በእርሱ ላይ እጽፋለሁ።
13Kas turi ausis, teklauso, ką Dvasia sako bažnyčioms!”
13መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
14“Laodikėjos bažnyčios angelui rašyk: ‘Tai skelbia Amen, ištikimasis ir tikrasis Liudytojas, Dievo kūrinijos pradžia.
14በሎዶቅያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። አሜን የሆነው፥ የታመነውና እውነተኛው ምስክር፥ በእግዚአብሔርም ፍጥረት መጀመሪያ የነበረው እንዲህ ይላል።
15Žinau tavo darbus, jog esi nei šaltas, nei karštas. O, kad būtum arba šaltas, arba karštas!
15በራድ ወይም ትኩስ እንዳይደለህ ሥራህን አውቃለሁ። በራድ ወይም ትኩስ ብትሆንስ መልካም በሆነ ነበር።
16Bet kadangi esi drungnas ir nei karštas, nei šaltas, Aš išspjausiu tave iš savo burnos.
16እንዲሁ ለብ ስላልህ በራድም ወይም ትኩስ ስላልሆንህ ከአፌ ልተፋህ ነው።
17Tu gi sakai: ‘Aš esu turtingas ir pralobęs, ir nieko man nebereikia’,o nežinai, kad esi skurdžius, apgailėtinas, beturtis, aklas ir nuogas.
17ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ፥
18Aš tau patariu pirkti iš manęs išgryninto ugnyje aukso, kad pralobtum, baltus drabužius, kad apsirengtum ir nebūtų matoma tavo nuogumo gėda, ir tepalo pasitepti akims, kad praregėtum.
18ባለ ጠጋ እንድትሆን በእሳት የነጠረውን ወርቅ፥ ተጐናጽፈህም የራቁትነትህ ኃፍረት እንዳይገለጥ ነጭ ልብስን፥ እንድታይም ዓይኖችህን የምትኳለውን ኵል ከእኔ ትገዛ ዘንድ እመክርሃለሁ።
19Tuos, kuriuos myliu, Aš baru ir drausminu; būk tad uolus ir atgailauk!
19እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገሥጻቸዋለሁ እቀጣቸውማለሁ፤ እንግዲህ ቅና ንስሐም ግባ።
20Štai Aš stoviu prie durų ir beldžiu: jei kas išgirs mano balsą ir atvers duris, Aš pas jį užeisiu ir vakarieniausiu su juo, o jis su manimi.
20እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ፥ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል።
21Nugalėtojui Aš duosiu atsisėsti šalia savęs, savo soste, kaip ir Aš nugalėjau ir atsisėdau šalia savo Tėvo, Jo soste’.
21እኔ ደግሞ ድል እንደ ነሣሁ ከአባቴም ጋር በዙፋኑ ላይ እንደተቀመጥሁ፥ ድል ለነሣው ከእኔ ጋር በዙፋኔ ላይ ይቀመጥ ዘንድ እሰጠዋለሁ።
22Kas turi ausis, teklauso, ką Dvasia sako bažnyčioms!”
22መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።