Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

4

1Paskui aš pažiūrėjau, ir štai atvertos durys danguje, ir pirmasis balsas, kurį girdėjau gaudžiant tarsi trimitą, kalbėjo: “Užženk čionai, ir tau parodysiu, kas toliau turi įvykti”.
1ከዚያ በኋላም አየሁ፥ እነሆም በሰማይ የተከፈተ ደጅ፥ እንደ መለከትም ሆኖ ሲናገረኝ የሰማሁት ፊተኛው ድምፅ። ወደዚህ ውጣና ከዚህ በኋላ ሊሆን የሚያስፈልገውን ነገር አሳይሃለሁ አለ።
2Bematant mane ištiko Dvasios pagava. Ir štai danguje buvo sostas, o soste­Sėdintysis.
2ወዲያው በመንፈስ ነበርሁ፤ እነሆም፥ ዙፋን በሰማይ ቆሞአል በዙፋኑም ላይ ተቀማጭ ነበረ፤
3Jo išvaizda buvo panaši į jaspio ir sardžio brangakmenius, o vaivorykštė, juosianti sostą, buvo panaši į smaragdą.
3ተቀምጦም የነበረው በመልኩ የኢያስጲድንና የሰርዲኖን ዕንቍ ይመስል ነበር። በመልኩም መረግድን የመሰለ ቀስተ ደመና በዙፋኑ ዙሪያ ነበረ።
4Aplinkui sostą regėjau dvidešimt keturis sostus ir tuose sostuose sėdinčius dvidešimt keturis vyresniuosius baltais drabužiais, o jų galvas puošė aukso vainikai.
4በዙፋኑ ዙሪያም ሀያ አራት ዙፋኖች ነበሩ፥ በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው በራሳቸውም የወርቅ አክሊል ደፍተው ሀያ አራት ሽማግሌዎች ተቀምጠው ነበር።
5Nuo sosto ėjo žaibai, aidėjo balsai ir griaustiniai; septyni deglai liepsnojo prieš sostą, o tai yra septynios Dievo Dvasios.
5ከዙፋኑም መብረቅና ድምፅ ነጐድጓድም ይወጣል፤ በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር፥ እነርሱም ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው።
6Prieš sostą tviskėjo tarsi stiklo jūra, panaši į krištolą; sosto viduryje ir aplinkui sostą buvo keturios būtybės, pilnos akių iš priekio ir iš užpakalio.
6በዙፋኑም ፊት ብርሌ የሚመስል የብርጭቆ ባሕር ነበረ። በዙፋኑም መካከል በዙፋኑም ዙሪያ፥ በፊትና በኋላ ዓይኖች የሞሉአቸው አራት እንስሶች ነበሩ።
7Pirmoji būtybė buvo panaši į liūtą, antroji būtybė panaši į veršį, trečioji būtybė turinti tartum žmogaus veidą, ketvirtoji būtybė panaši į skrendantį erelį.
7ፊተኛውም እንስሳ አንበሳን ይመስላል፥ ሁለተኛውም እንስሳ ጥጃን ይመስላል፥ ሦስተኛውም እንስሳ እንደ ሰው ፊት ነበረው፥ አራተኛውም እንስሳ የሚበረውን ንስር ይመስላል።
8Kiekviena iš keturių būtybių turėjo po šešis sparnus; aplinkui ir viduryje jos buvo pilnos akių. Ir be paliovos, dieną ir naktį, jos šaukė: “Šventas, šventas, šventas, Viešpats, visagalis Dievas, kuris buvo, kuris yra ir kuris ateina!”
8አራቱም እንስሶች እያንዳንዳቸው ስድስት ክንፎች አሉአቸው፥ በዙሪያቸውና በውስጣቸውም ዓይኖች ሞልተውባቸዋል፤ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም።
9Ir kiekvieną kartą, kai būtybės teikė Sėdinčiajam soste, Gyvenančiajam per amžių amžius, šlovę, pagarbą ir padėką,
9እንስሶቹም በዙፋን ላይ ለተቀመጠው ከዘላለምም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው ለእርሱ ክብርና ውዳሴ ምስጋናም በሰጡት ጊዜ፥
10dvidešimt keturi vyresnieji parpuldavo prieš Sėdintįjį soste, pagarbindavo Gyvenantįjį per amžių amžius ir numesdavo savo vainikus priešais sostą, sakydami:
10ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ። ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ።
11“Vertas esi, o Viešpatie, priimti šlovę, pagarbą ir jėgą, nes Tu visa sutvėrei­Tavo valia visa yra ir buvo sutverta”.