1Ir aš mačiau soste Sėdinčiojo dešinėje knygos ritinį, prirašytą iš vidaus ir iš viršaus, užantspauduotą septyniais antspaudais.
1በዙፋኑ ላይም በተቀመጠው በቀኝ እጁ ላይ በውስጥና በኋላ የተጻፈበት በሰባትም ማኅተም የተዘጋ መጽሐፍን አየሁ።
2Ir pamačiau galingą angelą, skelbiantį garsiu balsu: “Kas yra vertas atversti knygą ir nuplėšti nuo jos antspaudus?”
2ብርቱም መልአክ። መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ማኅተሞቹንም ይፈታ ዘንድ የሚገባው ማን ነው? ብሎ በታላቅ ድምፅ ሲያውጅ አየሁ።
3Bet niekas nei danguje, nei žemėje, nei po žeme negalėjo atversti knygos nei pažiūrėti į ją.
3በሰማይም ቢሆን በምድርም ላይ ቢሆን ከምድርም በታች ቢሆን መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው ማንም አልተቻለውም።
4Ir aš smarkiai verkiau, kad neatsirado verto atversti ir skaityti knygą ar pažiūrėti į ją.
4መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው የሚገባው ማንም ስላልተገኘ እጅግ አለቀስሁ።
5Tada vienas iš vyresniųjų man tarė: “Neverk! Štai nugalėjo liūtas iš Judo giminės, Dovydo atžala, kad atverstų knygą ir nuplėštų septynis jos antspaudus”.
5ከሽማግሌዎቹም አንዱ። አታልቅስ፤ እነሆ፥ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል አለኝ።
6Aš pažvelgiau, ir štai sosto ir keturių būtybių bei vyresniųjų viduryje stovėjo Avinėlis, tarytum užmuštas, turintis septynis ragus ir septynias akis, kurios yra septynios Dievo Dvasios, siųstos į visą žemę.
6በዙፋኑና በአራቱ እንስሶች መካከልም በሽማግሌዎችም መካከል እንደ ታረደ በግ ቆሞ አየሁ፥ ሰባትም ቀንዶችና ሰባት ዓይኖች ነበሩት እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ የተላኩ የእግዚአብሔር መናፍስት ናቸው።
7Jis priėjo ir paėmė knygą iš soste Sėdinčiojo dešinės.
7መጥቶም በዙፋን ላይ ከተቀመጠ ከዚያ ከቀኝ እጁ መጽሐፉን ወሰደው።
8Kai Jis paėmė knygą, keturios būtybės ir dvidešimt keturi vyresnieji parpuolė prieš Avinėlį, kiekvienas laikydamas rankose arfą ir aukso indus, pilnus smilkalų, kas yra šventųjų maldos.
8መጽሐፉንም በወሰደ ጊዜ አራቱ እንስሶችና ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በበጉ ፊት ወደቁ፥ እያንዳንዳቸውም በገናንና የቅዱሳን ጸሎት የሆነ ዕጣን የሞላበትን የወርቅ ዕቃ ያዙ።
9Ir jie giedojo naują giesmę, skelbdami: “Vertas esi paimti knygą ir atverti jos antspaudus, nes buvai užmuštas ir atpirkai Dievui savo krauju mus iš visų genčių, kalbų, tautų ir giminių.
9መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው፥ በምድርም ላይ ይነግሣሉ እያሉ አዲስን ቅኔ ይዘምራሉ።
10Ir iš mūsų padarei mūsų Dievui karalystę bei kunigus, ir mes viešpatausime žemėje”.
11አየሁም፥ በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር፥
11Aš pažvelgiau ir išgirdau balsą daugybės angelų aplinkui sostą, būtybių ir vyresniųjų; jų skaičius buvo miriadų miriadai ir tūkstančių tūkstančiai.
12በታላቅም ድምፅ። የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል አሉ።
12Jie skelbė skambiu balsu: “Vertas Avinėlis, kuris buvo užmuštas, priimti galybę, ir turtus, ir išmintį, ir stiprybę, ir pagarbą, ir šlovę, ir palaiminimą”.
13በሰማይና በምድርም ከምድርም በታች በባሕርም ላይ ያለ ፍጥረት ሁሉ በእነርሱም ውስጥ ያለ ሁሉ። በረከትና ክብር ምስጋናም ኃይልም ከዘላለም እስከ ዘላለም በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው፥ ለበጉም ይሁን ሲሉ ሰማሁ።
13Ir girdėjau, kaip visi tvariniai, esantys danguje, žemėje, po žeme ir jūroje, ir visa, kas juose yra, skelbė: “Sėdinčiajam soste ir Avinėliui tebūnie palaiminimas, ir pagarba, ir šlovė, ir valdžia per amžių amžius!”
14አራቱም እንስሶች። አሜን አሉ፥ ሽማግሌዎቹም ወድቀው ሰገዱ።
14Keturios būtybės sakė: “Amen!”, o dvidešimt keturi vyresnieji puolė ant žemės ir pagarbino Gyvenantįjį per amžių amžius.