1Ir aš pamačiau naują dangų ir naują žemę, nes pirmasis dangus ir pirmoji žemė praėjo ir jūros daugiau nebebuvo.
1አዲስ ሰማይንና አዲስ ምድርንም አየሁ፥ ፊተኛው ሰማይና ፊተኛይቱ ምድር አልፈዋልና፥ ባሕርም ወደ ፊት የለም።
2Ir aš, Jonas, išvydau šventąjį miestąnaująją Jeruzalę, nužengiančią iš dangaus nuo Dievo; ji buvo pasiruošusi kaip nuotaka, pasipuošusi savo sužadėtiniui.
2ቅድስቲቱም ከተማ አዲሲቱ ኢየሩሳሌም፥ ለባልዋ እንደ ተሸለመች ሙሽራ ተዘጋጅታ፥ ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አየሁ።
3Ir išgirdau galingą balsą, skambantį iš dangaus: “Štai Dievo buveinė tarp žmonių. Jis apsigyvens pas juos, ir jie bus Jo tauta, ir pats Dievas, jų Dievas, bus su jais.
3ታላቅም ድምፅ ከሰማይ። እነሆ፥ የእግዚአብሔር ድንኳን በሰዎች መካከል ነው ከእነርሱም ጋር ያድራል፥ እነርሱም ሕዝቡ ይሆናሉ እግዚአብሔርም እርሱ ራሱ ከእነርሱ ጋር ሆኖ አምላካቸው ይሆናል፤
4Jis nušluostys kiekvieną ašarą nuo jų akių; nebebus daugiau mirties, nei liūdesio, nei dejonės, nei skausmo daugiau nebebus, nes kas buvo pirmiaupraėjo”.
4እንባዎችንም ሁሉ ከዓይኖቻቸው ያብሳል፥ ሞትም ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፥ ኀዘንም ቢሆን ወይም ጩኸት ወይም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፥ የቀደመው ሥርዓት አልፎአልና ብሎ ሲናገር ሰማሁ።
5Ir Sėdintysis soste tarė: “Štai Aš visa darau nauja!” Jis pasakė man: “Rašyk, nes šitie žodžiai patikimi ir tikri”.
5በዙፋንም የተቀመጠው። እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ አለ። ለእኔም። እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛዎች ናቸውና ጻፍ አለኝ።
6Ir Jis man pasakė: “Įvyko! Aš esu Alfa ir Omega, Pradžia ir Pabaiga. Trokštančiam Aš duosiu dovanai gerti iš gyvenimo vandens šaltinio.
6አለኝም። ተፈጽሞአል። አልፋና ዖሜጋ፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ። ለተጠማ ከሕይወት ውኃ ምንጭ እንዲያው እኔ እሰጣለሁ።
7Nugalėtojas paveldės viską, ir Aš būsiu jo Dievas, o jis bus mano sūnus.
7ድል የሚነሣ ይህን ይወርሳል አምላክም እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል።
8Bet bailiams, netikintiems, nešvankėliams, žudikams, ištvirkėliams, burtininkams, stabmeldžiams ir visiems melagiams skirta dalis ežere, kuris dega ugnimi ir siera; tai yra antroji mirtis”.
8ዳሩ ግን የሚፈሩና የማያምኑ የርኵሳንም የነፍሰ ገዳዮችም የሴሰኛዎችም የአስማተኛዎችም ጣዖትንም የሚያመልኩ የሐሰተኛዎችም ሁሉ ዕድላቸው በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው።
9Tada prie manęs priėjo vienas iš septynių angelų, turėjusių septynis dubenis, pilnus septynių paskutinių negandų, ir pasakė man: “Eikš, aš tau parodysiu nuotaką, Avinėlio sužadėtinę”.
9ሰባቱም ኋለኛዎች መቅሠፍቶች የሞሉባቸውን ሰባቱን ጽዋዎች ከያዙት ከሰባቱ መላእክት አንዱ መጥቶ። ወደዚህ ና፥ የበጉንም ሚስት ሙሽራይቱን አሳይሃለሁ ብሎ ተናገረኝ።
10Ir jis nunešė mane dvasioje ant didelio ir aukšto kalno, ir parodė man miestą, šventąją Jeruzalę, nusileidžiančią iš dangaus nuo Dievo,
10በመንፈስም ወደ ታላቅና ወደ ረጅም ተራራ ወሰደኝ፥ የእግዚአብሔርም ክብር ያለባትን ቅድስቲቱን ከተማ ኢየሩሳሌምን ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ፤ ብርሃንዋም እጅግ እንደ ከበረ ድንጋይ እንደ ኢያሰጲድ ድንጋይ ሆኖ እንደ ብርሌ የጠራ ነበረ፤
11žėrinčią Dievo šlove. Jos švytėjimas tarsi brangakmenio, tarsi jaspio akmens, tviskančio kaip krištolas.
12ታላቅና ረጅም ቅጥር ነበራት፥ አሥራ ሁለትም ደጆች ነበሩአት በደጆቹም አሥራ ሁለት መላእክት ቆሙ፥ የአሥራ ሁለቱም የእስራኤል ልጆች ነገዶች ስሞች ተጽፈውባቸው ነበር።
12Ji apjuosta didele ir aukšta siena su dvylika vartų, o ant vartų dvylika angelų ir užrašyti dvylikos Izraelio giminių vardai.
13በምሥራቅ ሦስት ደጆች፥ በሰሜንም ሦስት ደጆች፥ በደቡብም ሦስት ደጆች፥ በምዕራብም ሦስት ደጆች ነበሩ።
13Nuo rytų pusės treji vartai, nuo šiaurės treji vartai, nuo pietų treji vartai ir nuo vakarų treji vartai.
14ለከተማይቱም ቅጥር አሥራ ሁለት መሠረቶች ነበሩአት፥ በእነርሱም ውስጥ የአሥራ ሁለቱ የበጉ ሐዋርያት ስሞች ተጽፈው ነበር።
14Miesto sienos turi dvylika pamatų, ant kurių dvylikos Avinėlio apaštalų vardai.
15የተናገረኝም ከተማይቱንና ደጆችዋን ቅጥርዋንም ይለካ ዘንድ የወርቅ ዘንግ ነበረው።
15Kalbantysis su manimi turėjo matąauksinę nendrę išmatuoti miestui, jo vartams ir sienoms.
16ከተማይቱም አራት ማዕዘን ነበራት፥ ርዝመትዋም እንደ ስፋትዋ ልክ ነበረ። ከተማይቱንም በዘንግ ለካት አሥራ ሁለትም ሺህ ምዕራፍ ሆነች፤ ርዝመትዋና ስፋትዋ ከፍታዋም ትክክል ነው።
16Miestas išdėstytas keturkampiu: jo ilgis ir plotis lygūs. Jis išmatavo miestą nendre ir rado dvylika tūkstančių stadijų. Jo ilgis, plotis ir aukštis lygūs.
17ቅጥርዋንም ለካ፥ መቶ አርባ አራት ክንድ በሰው ልክ፥ እርሱም በመልአክ ልክ።
17Jis išmatavo jo sienas ir rado šimtą keturiasdešimt keturias uolektis žmonių mastu, tiek pat ir angelo mastu.
18ቅጥርዋም ከኢያሰጲድ የተሠራ ነበረ፥ ከተማይቱም ጥሩ ብርጭቆ የሚመስል ጥሩ ወርቅ ነበረች።
18Jo sienos sukrautos iš jaspio, o pats miestas iš gryno aukso, panašaus į vaiskų stiklą.
19የከተማይቱም ቅጥር መሠረት በከበረ ድንጋይ ሁሉ ተጌጦ ነበር፤ ፊተኛው መሠረት ኢያሰጲድ፥ ሁለተኛው ሰንፔር፥ ሦስተኛው ኬልቄዶን፥ አራተኛው መረግድ፥
19Miesto sienų pamatai papuošti visokiais brangakmeniais. Pirmas pamatas yra jaspio, antras safyro, trečias chalcedono, ketvirtas smaragdo,
20አምስተኛው ሰርዶንክስ፥ ስድስተኛው ሰርድዮን፥ ሰባተኛው ክርስቲሎቤ፥ ስምንተኛው ቢረሌ፥ ዘጠነኛው ወራውሬ፥ አሥረኛው ክርስጵራስስ፥ አሥራ አንደኛው ያክንት፥ አሥራ ሁለተኛው አሜቴስጢኖስ ነበረ።
20penktas sardonikso, šeštas sardžio, septintas chrizolito, aštuntas berilio, devintas topazo, dešimtas chrizoprazo, vienuoliktas hiacinto, dvyliktas ametisto.
21አሥራ ሁለቱም ደጆች አሥራ ሁለት ዕንቆች ነበሩ፤ እየአንዳንዱ ደጅ ከአንድ ዕንቍ የተሠራ ነበረ። የከተማይቱም አደባባይ ጥሩ ብርጭቆ የሚመስል ጥሩ ወርቅ ነበረ።
21Dvylika vartųdvylika perlų, kiekvieni vartai iš vieno perlo. Ir miesto gatvėsgrynas auksas, tarsi vaiskus stiklas.
22ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክና በጉ መቅደስዋ ናቸውና መቅደስ በእርስዋ ዘንድ አላየሁም።
22Bet jame nemačiau šventyklos, nes Viešpats, visagalis Dievas, ir Avinėlis yra jo šventykla.
23ለከተማይቱም የእግዚአብሔር ክብር ስለሚያበራላት መብራትዋም በጉ ስለ ሆነ፥ ፀሐይ ወይም ጨረቃ እንዲያበሩላት አያስፈልጓትም ነበር።
23Miestui apšviesti nereikia nei saulės, nei mėnulio, nes jame šviečia Dievo šlovė ir jo žiburys yra Avinėlis.
24አሕዛብም በብርሃንዋ ይመላለሳሉ፥ የምድርም ነገሥታት ክብራቸውን ወደ እርስዋ ያመጣሉ፤
24Ir išgelbėtos tautos vaikščios jo šviesoje, ir žemės karaliai atsineš į jį savo šlovę ir garbę.
25በዚያም ሌሊት ስለሌለ ደጆችዋ በቀን ከቶ አይዘጉም፥
25Jo vartai nebus uždaromi dieną,nes tenai nebus nakties,
26የአሕዛብንም ግርማና ክብር ወደ እርስዋ ያመጣሉ።
26ir į jį bus atnešta tautų šlovė ir garbė.
27ለበጉም በሆነው በሕይወት መጽሐፍ ከተጻፉት በቀር፥ ጸያፍ ነገር ሁሉ ርኵሰትና ውሸትም የሚያደርግ ወደ እርስዋ ከቶ አይገባም።
27Ir ten niekados nepateks, kas netyra, joks nešvankėlis ar melagis, o tiktai tie, kurie įrašyti Avinėlio gyvenimo knygoje.