Lithuanian

Amharic: New Testament

Revelation

22

1Jis parodė man tyrą gyvenimo vandens upę, tvaskančią tarsi krištolas, ištekančią nuo Dievo ir Avinėlio sosto.
1በአደባባይዋም መካከል ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን የሚወጣውን እንደ ብርሌ የሚያንጸባርቀውን የሕይወትን ውኃ ወንዝ አሳየኝ።
2Viduryje miesto gatvės, abejose upės pusėse, augo gyvenimo medis, duodantis dvylika derlių, kiekvieną mėnesį vedantis vaisių, o to medžio lapai­tautoms gydyti.
2በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።
3Ir nebus daugiau jokio prakeikimo. Mieste stovės Dievo ir Avinėlio sostas, ir Jo tarnai tarnaus Jam.
3ከእንግዲህም ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም። የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል፥ ባሪያዎቹም ያመልኩታል፥ ፊቱንም ያያሉ፥
4Jie regės Jo veidą, ir jų kaktose bus Jo vardas.
4ስሙም በግምባሮቻቸው ይሆናል።
5Ten nebebus nakties, jiems nereikės nei žiburio, nei saulės šviesos, nes Viešpats Dievas jiems švies, ir jie viešpataus per amžių amžius.
5ከእንግዲህም ወዲህ ሌሊት አይሆንም፥ ጌታ አምላክም በእነርሱ ላይ ያበራላቸዋልና የመብራት ብርሃንና የፀሐይ ብርሃን አያስፈልጋቸውም፤ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ይነግሣሉ።
6Tuomet jis man pasakė: “Šie žodžiai patikimi ir tikri. Viešpats, šventų pranašų Dievas, atsiuntė savo angelą parodyti savo tarnams, kas turi įvykti netrukus”.
6እርሱም። እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛዎች ናቸው፥ የነቢያትም መናፍስት ጌታ አምላክ በቶሎ ሊሆን የሚገባውን ነገር ለባሪያዎቹ እንዲያሳይ መልአኩን ሰደደ።
7“Štai Aš veikiai ateinu! Palaimintas, kas laikosi šios knygos pranašystės žodžių!”
7እነሆም፥ በቶሎ እመጣለሁ። የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል የሚጠብቅ ብፁዕ ነው አለኝ።
8Aš, Jonas, visa tai mačiau ir girdėjau. Išgirdęs ir pamatęs, puoliau po kojų angelui, kuris man visa tai parodė, norėdamas jį pagarbinti.
8ይህንም ያየሁትና የሰማሁት እኔ ዮሐንስ ነኝ። በሰማሁትና ባየሁትም ጊዜ ይህን ባሳየኝ በመልአኩ እግር ፊት እሰግድ ዘንድ ተደፋሁ።
9Bet jis man pasakė: “Žiūrėk, kad to nedarytum! Juk ir aš esu tarnas, kaip tu ir tavo broliai pranašai, ir visi, kurie laikosi šios knygos žodžių. Dievą garbink!”
9እርሱም። እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር ከወንድሞችህም ከነቢያት ጋር የዚህንም መጽሐፍ ቃል ከሚጠብቁ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ አለኝ።
10Jis sako man: “Neužantspauduok pranašiškų šios knygos žodžių, nes laikas trumpas.
10ለእኔም። ዘመኑ ቀርቦአልና የዚህን መጽሐፍ ትንቢት ቃል በማኅተም አትዝጋው።
11Neteisusis toliau tesielgia neteisiai, kas susitepęs, ir toliau tebūna susitepęs, teisusis toliau tevykdo teisumą, ir šventasis dar tepašventėja”.
11ዓመፀኛው ወደ ፊት ያምፅ፥ ርኵሱም ወደ ፊት ይርከስ፥ ጻድቁም ወደ ፊት ጽድቅ ያድርግ፥ ቅዱሱም ወደፊት ይቀደስ አለ።
12“Štai Aš veikiai ateinu, ir mano atlygis su manimi, kad kiekvienam atlyginčiau pagal jo darbus.
12እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ።
13Aš esu Alfa ir Omega, Pradžia ir Pabaiga, Pirmasis ir Paskutinysis”.
13አልፋና ዖሜጋ፥ ፊተኛውና ኋለኛው፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ።
14“Palaiminti, kurie vykdo Jo įsakymus, kad įgytų teisę į gyvenimo medį ir galėtų įžengti pro vartus į miestą.
14ወደ ሕይወት ዛፍ ለመድረስ ሥልጣን እንዲኖራቸው በደጆችዋም ወደ ከተማይቱም እንዲገቡ ልብሳቸውን የሚያጥቡ ብፁዓን ናቸው።
15O lauke lieka šunys, burtininkai, ištvirkėliai, žudikai, stabmeldžiai ir visi, kurie mėgsta melą ir jį daro”.
15ውሻዎችና አስማተኞች ሴሰኛዎችም ነፍሰ ገዳዮችም ጣዖትንም የሚያመልኩት ውሸትንም የሚወዱና የሚያደርጉ ሁሉ በውጭ አሉ።
16“Aš, Jėzus, pasiunčiau savo angelą jums tai paliudyti apie bažnyčias. Aš esu Dovydo šaknis ir palikuonis, žėrinti aušrinė žvaigždė!”
16እኔ ኢየሱስ በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ይህን እንዲመሰክርላችሁ መልአኬን ላክሁ። እኔ የዳዊት ሥርና ዘር ነኝ፥ የሚያበራም የንጋት ኮከብ ነኝ።
17Ir Dvasia, ir sužadėtinė kviečia: “Ateik!” Ir kas girdi, teatsiliepia: “Ateik!” Ir kas trokšta, teateina, ir kas nori, tesisemia dovanai gyvenimo vandens.
17መንፈሱና ሙሽራይቱም። ና ይላሉ። የሚሰማም። ና ይበል። የተጠማም ይምጣ፥ የወደደም የሕይወትን ውኃ እንዲያው ይውሰድ።
18Aš sakau kiekvienam, kuris girdi šios knygos pranašystės žodžius: “Jeigu kas prie jų ką pridės­Dievas jam pridės aprašytų šioje knygoje negandų.
18በዚህ መጽሐፍ የተጻፈውን የትንቢት ቃል ለሚሰማ ሁሉ እኔ እመሰክራለሁ፤ ማንም በዚህ ላይ አንዳች ቢጨምር እግዚአብሔር በዚህ መጽሐፍ የተጻፉትን መቅሠፍቶች ይጨምርበታል፤
19Ir jeigu kas atims ką nors nuo šios pranašystės knygos žodžių­ Dievas atims jo dalį iš gyvenimo knygos ir šventojo miesto, kurie aprašyti šitoje knygoje”.
19ማንምም በዚህ በትንቢት መጽሐፍ ከተጻፉት ቃሎች አንዳች ቢያጎድል፥ በዚህ መጽሐፍ ከተጻፉት ከሕይወት ዛፍና ከቅድስቲቱ ከተማ እግዚአብሔር ዕድሉን ያጎድልበታል።
20Tas, kuris šitai liudija, sako: “Taip, Aš veikiai ateinu!” Amen. Taip, ateik, Viešpatie Jėzau!
20ይህን የሚመሰክር። አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።
21Mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus malonė su jumis visais! Amen!
21የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።