1gailestingumu aš prašau jus, broliai, aukoti savo kūnus kaip gyvą, šventą, Dievui patinkančią auką,tai jūsų sąmoningas tarnavimas.
1እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው።
2Ir neprisitaikykite prie šio pasaulio, bet pasikeiskite, atnaujindami savo protą, kad galėtumėte ištirti, kas yra gera, priimtina ir tobula Dievo valia.
2የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።
3Iš man suteiktos malonės raginu kiekvieną iš jūsų nemanyti apie save geriau negu dera manyti, bet manyti apie save blaiviai, pagal kiekvienam Dievo duotąjį tikėjimo saiką.
3እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ የእምነትን መጠን እንዳካፈለው፥ እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ጸጋ እናገራለሁ።
4Juk kaip viename kūne turime daug narių, bet ne visi nariai atlieka tą patį uždavinį,
4በአንድ አካል ብዙ ብልቶች እንዳሉን፥ የብልቶቹም ሁሉ ሥራ አንድ እንዳይደለ፥
5taip ir mūsų daugybė yra vienas kūnas Kristuje, o pavieniuivieni kitų nariai.
5እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን፥ እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን።
6Pagal mums suteiktą malonę turime įvairių dovanų. Jei kas turi pranašavimą, tepranašauja pagal tikėjimo saiką;
6እንደ ተሰጠንም ጸጋ ልዩ ልዩ ስጦታ አለን፤ ትንቢት ቢሆን እንደ እምነታችን መጠን ትንቢት እንናገር፤
7jei kas turi tarnavimątetarnauja; kas mokymątemoko;
7አገልግሎት ቢሆን በአገልግሎታችን እንትጋ፤ የሚያስተምርም ቢሆን በማስተማሩ ይትጋ፤
8kas skatinimąteskatina; kas duodatedaro tai iš atviros širdies; kas vadovaujatevadovauja uoliai; kas daro gailestingumo darbustedaro tai su džiaugsmu.
8የሚመክርም ቢሆን በመምከሩ ይትጋ፤ የሚሰጥ በልግስና ይስጥ፤ የሚገዛ በትጋት ይግዛ፤ የሚምር በደስታ ይማር።
9Meilė tebūna neveidmainiška. Venkite pikto, laikykitės gero.
9ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን። ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤
10Švelniai mylėkite vienas kitą broliška meile; pagarbiai vertinkite kitus aukščiau nei save.
10በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤
11Uolumu nebūkite tingūs; būkite liepsnojančios dvasios, tarnaukite Viešpačiui.
11ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤
12Džiaukitės viltimi, būkite kantrūs išmėginimuose, nepaliaujamai melskitės.
12በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤
13Dalinkitės šventųjų poreikiais, puoselėkite svetingumą.
13ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ።
14Laiminkite savo persekiotojus, laiminkite, o ne keikite.
14የሚያሳድዱአችሁን መርቁ፥ መርቁ እንጂ አትርገሙ።
15Džiaukitės su besidžiaugiančiais, verkite su verkiančiais.
15ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።
16Būkite vienminčiai tarpusavyje. Negalvokite apie didelius dalykus, bet sekite nuolankiaisiais. Nebūkite išmintingi savo akyse.
16እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ፤ የትዕቢትን ነገር አታስቡ፥ ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ። ልባሞች የሆናችሁ አይምሰላችሁ።
17Niekam neatmokėkite piktu už pikta, rūpinkitės tuo, kas dora visų žmonių akyse.
17ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ።
18Kiek įmanoma ir kiek nuo jūsų priklauso, gyvenkite taikingai su visais žmonėmis.
18ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።
19Nekeršykite patys, mylimieji, bet palikite tai rūstybei, nes parašyta: “Mano kerštas, Aš atmokėsiu”,sako Viešpats.
19ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።
20Todėl, jei tavo priešininkas alkanas, pavalgydink jį, jei trokšta, pagirdyk jį. Taip darydamas, tu sukrausi žarijas ant jo galvos.
20ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና።
21Nesiduok pikto nugalimas, bet nugalėk pikta gerumu.
21ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።