1Tad aš klausiu: ar Dievas atstūmė savo tautą? Jokiu būdu! Juk ir aš izraelitas, iš Abraomo palikuonių, iš Benjamino giminės.
1እንግዲህ። እግዚአብሔር ሕዝቡን ጣላቸውን? እላለሁ። አይደለም እኔ ደግሞ እስራኤላዊና ከአብርሃም ዘር ከብንያምም ወገን ነኝና።
2Dievas neatstūmė savosios tautos, kurią iš anksto numatė. Ar nežinote, ką sako Raštas apie Eliją, kai šis skundžiasi Izraeliu:
2እግዚአብሔር አስቀድሞ ያወቃቸውን ሕዝብ አልጣላቸውም። መጽሐፍ ስለ ኤልያስ በተጻፈው የሚለውን፥ በእግዚአብሔር ፊት እስራኤልን እንዴት እንደሚከስ፥ አታውቁምን?
3“Viešpatie, jie išžudė Tavo pranašus, išgriovė Tavo aukurus; aš vienas belikau, ir jie tyko mano gyvybės”.
3ጌታ ሆይ፥ ነቢያትህን ገደሉ መሠዊያዎችህንም አፈረሱ እኔም ብቻዬን ቀረሁ ነፍሴንም ይሹአታል።
4O kaip skamba Dievo atsakymas? “Aš pasilaikiau septynis tūkstančius vyrų, kurie nesulenkė kelių prieš Baalį”.
4ነገር ግን አምላካዊ መልስ ምን አለው? ለበአል ያልሰገዱትን ሰባት ሺህ ሰዎች ለእኔ አስቀርቼአለሁ።
5Ir dabartiniu metu yra malonės išrinktas likutis.
5እንደዚሁም በአሁን ዘመን ደግሞ በጸጋ የተመረጡ ቅሬታዎች አሉ።
6Ir jei malone, tai ne dėl darbų, nes tada malonė nebūtų malonė. Bet jeigu darbais, tai jau nebus malonė; kitaip darbas nebūtų darbas.
6በጸጋ ከሆነ ግን ከሥራ መሆኑ ቀርቶአል፤ ጸጋ ያለዚያ ጸጋ መሆኑ ቀርቶአል።
7Tai ką gi? Izraelis nepasiekė to, ko ieškojo. Pasiekė tiktai išrinktoji dalis. Kiti buvo apakinti,
7እንግዲህ ምንድር ነው? እስራኤል የሚፈልጉትን አላገኙትም፤ የተመረጡት ግን አገኙት፤
8kaip parašyta: “Dievas jiems siuntė snaudulio dvasią, kad akys neregėtų ir ausys negirdėtų iki šios dienos”.
8ሌሎቹም ደነዘዙ፤ እንዲሁም። ዓይኖቻቸው እንዳያዩ ጆሮቻቸውም እንዳይሰሙ እግዚአብሔር የእንቅልፍ መንፈስን እስከ ዛሬ ድረስ ሰጣቸው ተብሎ ተጽፎአል። ዳዊትም።
9Ir Dovydas sako: “Jų stalas tepavirsta jiems spąstais, žabangais, suklupimo akmeniu ir atpildu.
9ማዕዳቸው ወጥመድና አሽክላ ማሰናከያም ፍዳም ይሁንባቸው፤
10Tegul aptemsta jų akys, kad neregėtų, ir jų nugarą laikyk nuolat sulenktą”.
10ዓይኖቻቸው እንዳያዩ ይጨልሙ፥ ጀርባቸውንም ዘወትር አጉብጥ ብሎአል።
11Tad aš klausiu: negi izraelitai taip suklupo, kad pargriūtų? Jokiu būdu! Tik per jų suklupimą pagonims atėjo išgelbėjimas, kad juos paimtų pavydas.
11እንግዲህ። የተሰናከሉ እስኪወድቁ ድረስ ነውን? እላለሁ። አይደለም፤ ነገር ግን እነርሱን ያስቀናቸው ዘንድ በእነርሱ በደል መዳን ለአሕዛብ ሆነ።
12Bet jeigu jų suklupimas yra pasauliui praturtinimas ir jų sumažėjimaspagonims praturtinimas, tai ką duos jų visuma?
12ዳሩ ግን በደላቸው ለዓለም ባለ ጠግነት መሸነፋቸውም ለአሕዛብ ባለ ጠግነት ከሆነ፥ ይልቁንስ መሙላታቸው እንዴት ይሆን?
13Jums, pagonims, sakau: būdamas pagonių apaštalas, aš gerbiu savo tarnavimą:
13ለእናንተም ለአሕዛብ እናገራለሁ። እኔ የአሕዛብ ሐዋርያ በሆንሁ መጠን ሥጋዬ የሆኑትን አስቀንቼ ምናልባት ከእነርሱ አንዳንዱን አድን እንደሆነ አገልግሎቴን አከብራለሁ።
14gal kaip nors man pavyks sukelti savo tautiečių pavydą ir bent kai kuriuos išgelbėti.
15የእነርሱ መጣል ለዓለም መታረቅ ከሆነ ከሙታን ከሚመጣ ሕይወት በቀር መመለሳቸው ምን ይሆን?
15Jeigu jų atmetimas reiškia pasauliui sutaikinimą, tai ką gi reikštų jų priėmimas, jei ne gyvenimą iš numirusių?
16በኵራቱም ቅዱስ ከሆነ ብሆው ደግሞ ቅዱስ ነው፤ ሥሩም ቅዱስ ከሆነ ቅርንጫፎቹ ደግሞ ቅዱሳን ናቸው።
16Jei pirmieji vaisiai šventi, tai šventa ir visuma. Jei šaknis šventa, tai ir šakos.
17ነገር ግን ከቅርንጫፎች አንዳንዱ ቢሰበሩ አንተም የበረሀ ወይራ የሆንህ በመካከላቸው ገብተህ ከእነርሱ ጋር የወይራ ዘይት ከሚወጣው ሥር ተካፋይ ከሆንህ፥ በቅርንጫፎች ላይ አትመካ፤
17Jeigu kai kurios šakos buvo nulaužtos, o tulaukinis alyvmedisesi tarp jų įskiepytas ir tapęs šaknies bei alyvmedžio syvų dalininku,
18ብትመካባቸው ግን ሥሩ አንተን ይሸከምሃል እንጂ ሥሩን የምትሸከም አንተ አይደለህም።
18tai nesididžiuok prieš anas šakas! O jeigu didžiuojiesi, tai žinok, kad ne tu išlaikai šaknį, bet šaknis tave.
19እንግዲህ። እኔ እንድገባ ቅርንጫፎች ተሰበሩ ትል ይሆናል።
19Gal pasakysi: “Šakos nulaužtos tam, kad aš būčiau įskiepytas?”
20መልካም፤ እነርሱ ከአለማመን የተነሣ ተሰበሩ አንተም ከእምነት የተነሣ ቆመሃል። ፍራ እንጂ የትዕቢትን ነገር አታስብ።
20Gerai! Jos nulaužtos dėl netikėjimo, o tu stovi tikėjimu. Nesididžiuok, bet bijok!
21እግዚአብሔር እንደ ተፈጠሩት ለነበሩት ቅርንጫፎች የራራላቸው ካልሆነ ለአንተ ደግሞ አይራራልህምና።
21Jei Dievas nepagailėjo prigimtinių šakų, gali nepagailėti ir tavęs.
22እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ጭከና ተመልከት፤ ጭከናው በወደቁት ላይ ነው፥ በቸርነቱ ግን ጸንተህ ብትኖር የእግዚአብሔር ቸርነት በአንተ ላይ ነው፤ ያለዚያ አንተ ደግሞ ትቆረጣለህ።
22Taigi matai Dievo gerumą ir griežtumą: nupuolusiemsgriežtumas, o taugerumas, jei pasiliksi Jo gerume, kitaipir tu būsi iškirstas!
23እነዚያም ደግሞ በአለማመናቸው ጸንተው ባይኖሩ በዛፉ ውስጥ ይገባሉ፤ እግዚአብሔር መልሶ ሊያገባቸው ይችላልና።
23Bet ir anie, jei nepasiliks netikėjime, bus priskiepyti, nes Dievas turi galią ir vėl juos priskiepyti.
24አንተ በፍጥረቱ የበረሀ ከነበረ ወይራ ተቆርጠህ እንደ ፍጥረትህ ሳትሆን በመልካም ወይራ ከገባህ፥ ይልቁንስ እነዚያ በፍጥረታቸው ያሉት ቅርንጫፎች በራሳቸው ወይራ እንዴት አይገቡም?
24Tad jeigu buvai iškirstas iš prigimtojo laukinio alyvmedžio ir prieš prigimtį įskiepytas tauriajame alyvmedyje, tai juo labiau jie tikrosios šakosbus priskiepyti savajame alyvmedyje.
25ወንድሞች ሆይ፥ ልባሞች የሆናችሁ እንዳይመስላችሁ ይህን ምሥጢር ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ፤ የአሕዛብ ሙላት እስኪገባ ድረስ ድንዛዜ በእስራኤል በአንዳንድ በኩል ሆነባቸው፤
25Aš nenoriu, broliai, palikti jus nežinioje dėl šios paslapties,kad jūs per aukštai apie save nemanytumėte: dalis Izraelio užkietėjo, kol įeis pagonių visuma,
26እንደዚሁም እስራኤል ሁሉ ይድናል፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ። መድኃኒት ከጽዮን ይወጣል ከያዕቆብም ኃጢአተኛነትን ያስወግዳል።
26o tada bus išgelbėtas visas Izraelis, kaip parašyta: “Iš Siono ateis Gelbėtojas ir nukreips bedievystes nuo Jokūbo.
27ኃጢአታቸውንም ስወስድላቸው ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው።
27Tokia bus jiems mano sandora, kai nuimsiu jų nuodėmes”.
28በወንጌልስ በኩል ስለ እናንተ ጠላቶች ናቸው፥ በምርጫ በኩል ግን ስለ አባቶች ተወዳጆች ናቸው፤
28Žiūrint Evangelijos, jie yra Dievo priešai jūsų naudai; bet pagal išrinkimą jie numylėtiniai dėl savųjų tėvų.
29እግዚአብሔር በጸጋው ስጦታና በመጥራቱ አይጸጸትምና።
29Juk Dievo dovanos ir pašaukimasneatšaukiami.
30እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር እንዳልታዘዛችሁ፥ አሁን ግን ከአለመታዘዛቸው የተነሣ ምሕረት እንዳገኛችሁ፥
30Kaip jūs kadaise netikėjote Dievu, o dabar per jų netikėjimą patyrėte gailestingumą,
31እንዲሁ በተማራችሁበት ምሕረት እነርሱ ደግሞ ምሕረትን ያገኙ ዘንድ እነዚህ ደግሞ አሁን አልታዘዙም።
31taip ir jie dabar netiki, kad dėl jums suteikto pasigailėjimo ir jie susilauktų gailestingumo.
32እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።
32Dievas juos visus uždarė netikėjime, kad visų pasigailėtų.
33የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።
33O Dievo turtų, išminties ir pažinimo gelme! Kokie neištiriami Jo teismai ir nesusekami Jo keliai!
34የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው?
34“Ir kas gi pažino Viešpaties mintį? Ir kas buvo Jo patarėju?”
35ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው?
35“Arba kas Jam yra davęs pirmas, kad jam būtų atmokėta?”
36ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።
36Iš Jo, per Jį ir Jam yra visa. Jam šlovė per amžius! Amen.