Lithuanian

Amharic: New Testament

Romans

10

1Broliai, mano širdies troškimas ir malda Dievui yra už Izraelį,­kad jie išsigelbėtų.
1ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
2Aš jiems liudiju, kad jie turi uolumo Dievui, tačiau be pažinimo.
2በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
3Nesuprasdami Dievo teisumo ir bandydami įtvirtinti savąjį teisumą, jie nepakluso Dievo teisumui.
3የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
4Nes įstatymo pabaiga­Kristus, išteisinimui kiekvieno, kuris tiki.
4የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
5Mozė rašo apie teisumą iš įstatymo: “Jį vykdydamas žmogus juo gyvens”.
5ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
6Bet teisumas iš tikėjimo kalba taip: “Nesakyk savo širdyje: ‘Kas įžengs į dangų?’­tai yra Kristaus atsivesti;
6ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል። በልብህ። ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
7arba: ‘Kas nusileis į bedugnę?’­ tai yra Kristaus iš numirusių susigrąžinti”.
7ወይም። በልብህ። ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
8Bet ką jis sako?­“Arti tavęs yra žodis­tavo burnoje ir tavo širdyje”,­tai yra mūsų skelbiamas tikėjimo žodis.
8ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
9Jeigu lūpomis išpažinsi Viešpatį Jėzų ir širdimi tikėsi, kad Dievas Jį prikėlė iš numirusių, būsi išgelbėtas.
9ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
10Nes širdimi tikima, ir taip įgyjamas teisumas, o lūpomis išpažįstama, ir taip įgyjamas išgelbėjimas.
10ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
11Raštas juk sako: “Kiekvienas, kuris Jį tiki, nebus sugėdintas”.
11መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
12Nėra skirtumo tarp žydo ir graiko, nes tas pats Viešpats visiems, turtingas kiekvienam, kuris Jo šaukiasi,
12በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
13juk “kiekvienas, kuris šaukiasi Viešpaties vardo, bus išgelbėtas”.
13የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
14Kaip žmonės šauksis To, kurio neįtikėjo? Ir kaip jie įtikės Tą, apie kurį negirdėjo? Kaip išgirs be skelbėjo?
14እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?
15Ir kaip jie skelbs, jei nebus pasiųsti? Kaip parašyta: “Kokios puikios kojos tų, kurie skelbia ramybės Evangeliją, kurie neša geras žinias!”
15መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ?
16Bet ne visi pakluso Evangelijai. Nes Izaijas sako: “Viešpatie, kas patikėjo mūsų skelbimu?”
16ነገር ግን ሁሉ ለምሥራቹ ቃል አልታዘዙም። ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ምስክርነታችንን ማን አመነ? ብሎአልና።
17Taigi tikėjimas­iš klausymo, klausymas­iš Dievo žodžio.
17እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።
18Bet aš klausiu: argi jie negirdėjo? Kaipgi ne! “Po visą žemę pasklido jų garsas, ir jų žodžiai­iki pasaulio pakraščių”.
18ዳሩ ግን። ባይሰሙ ነው ወይ? እላለሁ። በእውነት። ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።
19Klausiu toliau: ar Izraelis nežinojo? Bet Mozė pirmas sako: “Aš sukelsiu jums pavydą per netautą, sukelsiu pyktį per neišmanančią tautą”.
19ነገር ግን። እስራኤል ባያውቁ ነው ወይ? እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ። እኔ ሕዝብ በማይሆነው አስቀናችኋለሁ በማያስተውልም ሕዝብ አስቆጣችኋለሁ
20Izaijas labai drąsiai sako: “Mane atrado tie, kurie manęs neieškojo, apsireiškiau tiems, kurie apie mane neklausinėjo”.
20ብሎአል። ኢሳይያስም ደፍሮ። ላልፈለጉኝ ተገኘሁ፥ ላልጠየቁኝም ተገለጥሁ አለ።
21Bet Izraeliui sako: “Ištisą dieną Aš laikiau ištiesęs savo rankas į neklusnią ir prieštaraujančią tautą”.
21ስለ እስራኤል ግን። ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ ይላል።