1Silpno tikėjimo žmogų priimkite, bet venkite ginčų dėl skirtingų nuomonių.
1በእምነት የደከመውንም ተቀበሉት፥ በአሳቡም ላይ አትፍረዱ።
2Vienas įsitikinęs, kad galima viską valgyti, o silpnas valgo tik daržoves.
2ሁሉን ይበላ ዘንድ እንደ ተፈቀደለት የሚያምን አለ፥ ደካማው ግን አትክልት ይበላል።
3Kuris valgo, teneniekina nevalgančio, o kuris nevalgo, teneteisia valgančio, nes Dievas jį priėmė.
3የሚበላ የማይበላውን አይናቀው የማይበላውም በሚበላው አይፍረድ፥ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና።
4Kas tu toks, kad drįsti teisti kito tarną?! Ar jis stovi, ar krentatai savajam Viešpačiui. Bet jis stovės, nes Dievas turi galią jį išlaikyti.
4አንተ በሌላው ሎሌ የምትፈርድ ማን ነህ? እርሱ ቢቆም ወይም ቢወድቅ ለገዛ ጌታው ነው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊያቆመው ይችላልና ይቆማል።
5Vienas išskiria vieną dieną iš kitų dienų, o kitam jos visos vienodos. Kiekvienas tebūna įsitikinęs pagal savo išmanymą.
5ይህ ሰው አንድ ቀን ከሌላ ቀን እንዲሻል ያስባል፥ ያ ግን ቀን ሁሉ አንድ እንደ ሆነ ያስባል፤ እያንዳንዱ በገዛ አእምሮው አጥብቆ ይረዳ።
6Tas, kuris išskiria dieną, daro tai Viešpačiui, ir tas, kuris neišskiria dienos, nesilaiko jos Viešpačiui. Tas, kuris valgovalgo Viešpačiui, nes jis dėkoja Dievui, o tas, kuris nevalgonevalgo Viešpačiui ir dėkoja Dievui.
6ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል፤ የሚበላም እግዚአብሔርን ያመሰግናልና ለጌታ ብሎ ይበላል፤ የማይበላም ለጌታ ብሎ አይበላም እግዚአብሔርንም ያመሰግናል።
7Nė vienas iš mūsų negyvena sau ir nė vienas sau nemiršta.
7ከእኛ አንድ ስንኳ ለራሱ የሚኖር የለምና፥ ለራሱም የሚሞት የለም፤
8Jei mes gyvename, gyvename Viešpačiui, ir jeigu mirštame, Viešpačiui mirštame. Todėl, ar mes gyvename, ar mirštame, esame Viešpaties.
8በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፥ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን።
9Nes dėl to Kristus ir mirė, ir prisikėlė, ir atgijo, kad būtų ir mirusiųjų, ir gyvųjų Viešpats.
9ስለዚህ ነገር ሙታንንም ሕያዋንንም ይገዛ ዘንድ ክርስቶስ ሞቶአልና ሕያውም ሆኖአልና።
10Tai kodėl gi tu teisi savo brolį? Arba kodėl niekini savo brolį? Juk mes visi stosime prieš Kristaus teismo krasę.
10አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና።
11Parašyta: “Kaip Aš gyvas,sako Viešpats,prieš mane suklups kiekvienas kelis, ir kiekvienos lūpos išpažins Dievą”.
11እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና።
12Taigi kiekvienas iš mūsų duos Dievui apyskaitą už save.
12እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።
13Tad liaukimės teisti vieni kitus. Verčiau nuspręskime neduoti broliui akstino nupulti ar pasipiktinti.
13እንግዲህ ከዛሬ ጀምሮ እርስ በርሳችን አንፈራረድ፤ ይልቁን ግን ለወንድም እንቅፋትን ወይም ማሰናከያን ማንም እንዳያኖርበት ይህን ቍረጡ።
14Žinau ir esu įsitikinęs Viešpatyje Jėzuje, kad nieko nėra savaime netyro. Bet tam, kas mano esant netyrų dalykų, tam jie netyri.
14በራሱ ርኵስ የሆነ ነገር እንደ ሌለ በጌታ በኢየሱስ ሆኜ አውቄአለሁ ተረድቼአለሁም፤ ነገር ግን ምንም ርኵስ እንዲሆን ለሚቆጥር ለእርሱ ርኵስ ነው።
15Jei tavo brolis įsižeidžia dėl maisto, tu jau nebesielgi iš meilės. Savo maistu nežlugdyk to, už kurį mirė Kristus!
15ወንድምህንም በመብል ምክንያት የምታሳዝን ከሆንህ እንግዲህ በፍቅር አልተመላለስህም። ክርስቶስ ስለ እርሱ የሞተለትን እርሱን በመብልህ አታጥፋው።
16Jūsų gėris tegul nebūna akstinas piktžodžiauti.
16እንግዲህ ለእናንተ ያለው መልካም ነገር አይሰደብ፤
17Dievo karalystė nėra valgymas ir gėrimas, bet teisumas, ramybė ir džiaugsmas Šventojoje Dvasioje.
17የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና።
18Kas taip Kristui tarnauja, tas priimtinas Dievui ir vertas žmonių pritarimo.
18እንደዚህ አድርጎ ለክርስቶስ የሚገዛ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛልና፥ በሰውም ዘንድ የተመሰገነ ነው።
19Tad siekime to, kas atneša ramybę ir pasitarnauja tarpusavio ugdymui.
19እንግዲያስ ሰላም የሚቆምበትን እርስ በርሳችንም የምንታነጽበትን እንከተል።
20Negriauk Dievo darbo dėl maisto! Nors viskas tyra, bet yra bloga žmogui, kuris valgo kitų papiktinimui.
20በመብል ምክንያት የእግዚአብሔርን ሥራ አታፍርስ። ሁሉ ንጹሕ ነው፥ በመጠራጠር የተበላ እንደ ሆነ ግን ለዚያ ሰው ክፉ ነው።
21Gera yra nevalgyti mėsos, negerti vyno ir vengti visko, kas tavo brolį piktina, žeidžia ar silpnina.
21ሥጋን አለመብላት ወይንንም አለመጠጣት ወንድምህም የሚሰናከልበትን አለማድረግ መልካም ነው።
22Turi tikėjimą? Turėk jį sau, prieš Dievą. Laimingas tas, kuris nesmerkia savęs už tai, ką pasirenka.
22ለአንተ ያለህ እምነት በእግዚአብሔር ፊት ለራስህ ይሁንልህ። ፈትኖ መልካም እንዲሆን በሚቈጥረው ነገር በራሱ ላይ የማይፈርድ ብፁዕ ነው።
23O kas valgo abejodamas, tas smerktinas, nes valgo ne iš įsitikinimo. Visa, kas daroma ne iš įsitikinimo, yra nuodėmė.
23የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው።