Lithuanian

Amharic: New Testament

Romans

4

1O ką pasakysime gavus Abraomą­mūsų protėvį pagal kūną?
1እንግዲህ በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን?
2Jei Abraomas būtų buvęs išteisintas darbais, jis turėtų kuo pasigirti, tik ne prieš Dievą.
2አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢሆን የሚመካበት አለውና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም።
3Bet ką sako Raštas? “Abraomas patikėjo Dievu, ir tai jam buvo įskaityta teisumu”.
3መጽሐፍስ ምን አለ? አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት።
4Tam, kuris dirba, atlyginimas nelaikomas malone, bet skola.
4ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ ጸጋ አይቈጠርለትም፤
5O tam, kuris nedirba, bet tiki Tuo, kuris išteisina bedievį, jo tikėjimas įskaitomas jam teisumu.
5ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም በሚያደድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል።
6Taip ir Dovydas skelbia palaiminimą žmogui, kuriam Dievas be darbų įskaito teisumą:
6እንደዚህ ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቆጥርለት ስለ ሰው ብፅዕና ይናገራል እንዲህ ሲል።
7“Palaiminti, kurių nusikaltimai atleisti, kurių nuodėmės uždengtos;
7ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤
8palaimintas žmogus, kuriam Viešpats nuodėmės neįskaito!”
8ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።
9Ar šis palaiminimas taikomas tik apipjaustytiesiems, ar taip pat ir neapipjaustytiesiems? Mes sakėme, kad Abraomui tikėjimas buvo įskaitytas teisumu.
9እንግዲህ ይህ ብፅዕና ስለ መገረዝ ተነገረ? ወይስ ደግሞ ስለ አለመገረዝ? እምነቱ ለአብርሃም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት እንላለንና።
10Kokiu būdu? Jam esant apipjaustytam ar neapipjaustytam? Ne po apipjaustymo, bet prieš apipjaustymą.
10እንዴት ተቆጠረለት? ተገርዞ ሳለ ነውን? ወይስ ሳይገረዝ? ተገርዞስ አይደለም፥ ሳይገረዝ ነበር እንጂ።
11Jis gavo apipjaustymo žymę kaip antspaudą tikėjimo teisumo, kurį turėjo, būdamas dar neapipjaustytas. Taip jis tapo tėvu visiems tikintiesiems iš neapipjaustytųjų, kad ir jiems būtų įskaitytas teisumas,
11ሳይገረዝም በነበረው እምነት ያገኘው የጽድቅ ማኅተም የሆነ የመገረዝን ምልክት ተቀበለ፤ ይህም እነርሱ ደግሞ ጻድቃን ሆነው ይቆጠሩ ዘንድ ሳይገረዙ ለሚያምኑ ሁሉ አባት እንዲሆን ነው፥
12ir apipjaustymo tėvu tiems, kurie ne tik apipjaustyti, bet ir vaikšto mūsų tėvo Abraomo tikėjimo pėdomis, kurį jis turėjo, būdamas dar neapipjaustytas.
12ለተገረዙትም አባት እንዲሆን ነው፤ ይኸውም ለተገረዙት ብቻ አይደለም ነገር ግን አባታችን አብርሃም ሳይገረዝ የነበረውን የእምነቱን ፍለጋ ደግሞ ለሚከተሉ ነው።
13Ne įstatymu rėmėsi Abraomui arba jo palikuonims duotas pažadas, kad paveldės pasaulį, bet tikėjimo teisumu.
13የዓለምም ወራሽ እንዲሆን ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው የተስፋ ቃል በእምነት ጽድቅ ነው እንጂ በሕግ አይደለም።
14Jei paveldėtojai būtų tie, kurie remiasi įstatymu, tai tikėjimas būtų tuščias, o pažadas netektų vertės.
14ከሕግ የሆኑትስ ወራሾች ከሆኑ እምነት ከንቱ ሆኖአል የተስፋውም ቃል ተሽሮአል፤
15Juk įstatymą lydi baudžianti rūstybė, o kur nėra įstatymo, ten nėra ir nusižengimo.
15ሕጉ መቅሠፍትን ያደርጋልና፤ ነገር ግን ሕግ በሌለበት መተላለፍ የለም።
16Taigi paveldėjimas priklauso nuo tikėjimo, kad būtų iš malonės ir pažadas būtų tikras visiems palikuonims, ne tik tiems, kurie remiasi įstatymu, bet ir tiems, kurie turi tikėjimą Abraomo, kuris yra mūsų visų tėvas,
16ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም። ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው።
17kaip parašyta: “Aš padariau tave daugelio tautų tėvu”;­tėvas prieš Dievą, kuriuo jis tikėjo, kuris atgaivina mirusius, ir tai, ko nėra, vadina taip, lyg būtų.
18ዘርህ እንዲሁ ሊሆን ነው እንደ ተባለ፥ ተስፋ ባልሆነው ጊዜ የብዙ አሕዛብ አባት እንዲሆን ተስፋ ይዞ አመነ።
18Nesant jokios vilties, Abraomas patikėjo viltimi ir taip tapo daugelio tautų tėvu, kaip jam buvo pasakyta: “Tokie bus tavo palikuonys”.
19የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤
19Jis nepavargo tikėti ir nelaikė savo kūno apmirusiu (nors jam buvo apie šimtą metų) ir Saros įsčių apmirusiomis.
20ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም።
20Jis nepasidavė netikėjimui Dievo pažadu, bet buvo tvirtas tikėjime, teikdamas Dievui šlovę
22ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
21ir būdamas visiškai įsitikinęs, jog, ką Jis pažadėjo, įstengs ir įvykdyti.
23ነገር ግን። ተቈጠረለት የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ ስለ እኛም ነው እንጂ፤
22Todėl jam tai buvo įskaityta teisumu.
24ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታንችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው።
23Tačiau ne vien apie jį parašyta, kad “buvo įskaityta”,
24bet ir apie mus,­nes turės būti įskaityta ir mums, jei tikime Tą, kuris prikėlė iš numirusių Jėzų, mūsų Viešpatį,
25paaukotą dėl mūsų nusikaltimų ir prikeltą mums išteisinti.