Serbian: Cyrillic

Amharic: New Testament

Romans

7

1Или не знате, браћо (јер говорим онима који знају закон), да закон влада над човеком докле је жив?
1ወንድሞች ሆይ፥ ሕግን ለሚያውቁ እናገራለሁና ሰው ባለበት ዘመን ሁሉ ሕግ እንዲገዛው አታውቁምን?
2Јер је удата жена привезана законом за мужа докле год он живи; а ако ли муж њен умре, разреши се од закона мужевљег.
2ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖር ከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች።
3Зато, дакле, док јој је муж жив бива прељубочиница ако пође за другог мужа; а ако јој умре муж проста је од закона да не буде прељубочиница ако пође за другог.
3ስለዚህ ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ ትባላለች፤ ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ አይደለችም።
4Зато, браћо моја, и ви умресте закону телом Христовим, да будете другог, Оног што уста из мртвих, да плод донесемо Богу.
4እንዲሁ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ተገድላችኋል፤ ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ፥ እናንተ ለሌላው፥ ከሙታን ለተነሣው፥ ለእርሱ ትሆኑ ዘንድ።
5Јер кад бејасмо у телу, беху сласти греховне, које закон рађаху у удима нашим да се смрти плод доноси.
5በሥጋ ሳለን በሕግ የሚሆን የኃጢአት መሻት ለሞት ፍሬ ሊያፈራ በብልቶቻችን ይሠራ ነበርና፤
6А сад, умревши избависмо се од закона који нас држаше, да служимо Богу у обновљењу Духа а не у старини слова.
6አሁን ግን ለእርሱ ለታሰርንበት ስለ ሞትን፥ ከሕግ ተፈትተናል፥ ስለዚህም በአዲሱ በመንፈስ ኑሮ እንገዛለን እንጂ በአሮጌው በፊደል ኑሮ አይደለም።
7Шта ћемо дакле рећи? Је ли закон грех? Боже сачувај! Него ја греха не познах осим кроз закон; јер не знадох за жељу да закон не каза: Не зажели.
7እንግዲህ ምን እንላለን? ሕግ ኃጢአት ነውን? አይደለም፤ ነገር ግን በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ። አትመኝ ባላለ ምኞትን ባላወቅሁም ነበርና።
8А грех узе почетак кроз заповест, и начини у мени сваку жељу; јер је грех без закона мртав.
8ኃጢአት ግን ምክንያት አግኝቶ ምኞትን ሁሉ በትእዛዝ ሠራብኝ፤ ኃጢአት ያለ ሕግ ምውት ነውና።
9А ја живљах некад без закона; а кад дође заповест, онда грех оживе,
9እኔም ዱሮ ያለ ሕግ ሕያው ነበርሁ፤ ትእዛዝ በመጣች ጊዜ ግን ኃጢአት ሕያው ሆነ እኔም ሞትሁ፤
10А ја умрех, и нађе се да ми заповест би за смрт која беше дата за живот.
10ለሕይወትም የተሰጠችውን ትእዛዝ እርስዋን ለሞት ሆና አገኘኋት፤
11Јер грех узевши почетак кроз заповест превари ме, и уби ме њоме.
11ኃጢአት ምክንያት አግኝቶ በትእዛዝ አታሎኛልና በእርስዋም ገድሎኛል።
12Тако је, дакле, закон свет и заповест света и праведна и добра.
12ስለዚህ ሕጉ ቅዱስ ነው ትእዛዚቱም ቅድስትና ጻድቅት በጎም ናት።
13Добро ли дакле би мени смрт? Боже сачувај! Него грех, да се покаже грех добром чинећи ми смрт, да буде грех одвише грешан заповешћу.
13እንግዲህ በጎ የሆነው ነገር ለእኔ ሞት ሆነብኝን? አይደለም፥ ነገር ግን ኃጢአት ሆነ፤ ኃጢአትም በትእዛዝ ምክንያት ያለ ልክ ኃጢአተኛ ይሆን ዘንድ፥ ኃጢአትም እንዲሆን ይገለጥ ዘንድ በጎ በሆነው ነገር ለእኔ ሞትን ይሠራ ነበር።
14Јер знамо да је закон духован; а ја сам телесан, продан под грех:
14ሕግ መንፈሳዊ እንደ ሆነ እናውቃለንና፤ እኔ ግን ከኃጢአት በታች ልሆን የተሸጥሁ የሥጋ ነኝ።
15Јер не знам шта чиним, јер не чиним оно шта хоћу, него на шта мрзим оно чиним.
15የማደርገውን አላውቅምና፤ የምጠላውን ያን አደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን እርሱን አላደርገውም።
16Ако ли оно чиним шта нећу, хвалим закон да је добар.
16የማልወደውን ግን የማደርግ ከሆንሁ ሕግ መልካም እንደ ሆነ እመሰክራለሁ።
17А ово више ја не чиним него грех који живи у мени.
17እንደዚህ ከሆነ ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም፥ በእኔ የሚያድር ኃጢአት ነው እንጂ።
18Јер знам да добро не живи у мени, то јест у телу мом. Јер хтети имам у себи, али учинити добро не налазим.
18በእኔ ማለት በሥጋዬ በጎ ነገር እንዳይኖር አውቃለሁና፤ ፈቃድ አለኝና፥ መልካሙን ግን ማድረግ የለኝም።
19Јер добро што хоћу не чиним, него зло што нећу оно чиним.
19የማልወደውን ክፉን ነገር አደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን በጎውን ነገር አላደርገውም።
20А кад чиним оно што нећу, већ ја то не чиним него грех који живи у мени.
20የማልወደውን የማደርግ ከሆንሁ ግን ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም፥ በእኔ የሚኖር ኃጢአት ነው እንጂ።
21Налазим, дакле закон, кад хоћу добро да чиним, да ме на зло нагони.
21እንግዲያስ መልካሙን አደርግ ዘንድ ስወድ በእኔ ክፉ እንዲያድርብኝ ሕግን አገኛለሁ።
22Јер имам радост у закону Божијем по унутрашњем човеку;
22በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛልና፥
23Али видим други закон у удима својим, који се супроти закону ума мог, и заробљава ме законом греховним који је у удима мојим.
23ነገር ግን በብልቶቼ ከአእምሮዬ ሕግ ጋር የሚዋጋውንና በብልቶቼ ባለ በኃጢአት ሕግ የሚማርከኝን ሌላ ሕግ አያለሁ።
24Ја несрећни човек! Ко ће ме избавити од тела смрти ове?
24እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ! ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?
25Захваљујем Богу свом кроз Исуса Христа Господа нашег. Тако, дакле, ја сам умом својим служим закону Божијем а телом закону греховном.
25በኢየሱስ ክርስቶስ በጌታችን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። እንግዲያስ እኔ በአእምሮዬ ለእግዚአብሔር ሕግ፥ በሥጋዬ ግን ለኃጢአት ሕግ እገዛለሁ።