1እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።
1你們應該效法我,好像我效法基督一樣。
2ወንድሞች ሆይ፥ በሁሉ ስለምታስቡኝና አሳልፌ እንደ ሰጠኋችሁ ወግን ፈጽማችሁ ስለ ያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ።
2女人蒙頭的問題我稱讚你們,因為你們在一切事上都記念我,又持守我傳交給你們的教訓。
3ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ።
3但是我願意你們知道,基督是男人的頭,男人是女人的頭(“男人是女人的頭”或譯:“丈夫是妻子的頭”), 神是基督的頭。
4ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ ሁሉ ራሱን ያዋርዳል።
4男人禱告或講道的時候,如果蒙著頭,就是羞辱自己的頭。
5ራስዋን ሳትሸፍን ግን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራስዋን ታዋርዳለች፤ እንደ ተላጨች ያህል አንድ ነውና።
5女人禱告或講道的時候,如果不蒙著頭,就是羞辱自己的頭,因為這就好像剃了頭髮一樣。
6ሴትም ራስዋን ባትሸፍን ጠጉርዋን ደግሞ ትቆረጥ፤ ለሴት ግን ጠጉርዋን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ ራስዋን ትሸፍን።
6女人要不蒙著頭,她就應當把頭髮剪了;如果女人以為剪髮或剃頭是羞恥的事,她就應當蒙著頭。
7ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት።
7男人不應蒙著頭,因為他是 神的形象和榮耀,而女人是男人的榮耀。
8ሴት ከወንድ ናት እንጂ ወንድ ከሴት አይደለምና።
8因為男人不是由女人而出,女人卻是由男人而出,
9ሴት ስለ ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ ስለ ሴት አልተፈጠረምና።
9並且男人不是為了女人而造的,女人卻是為了男人而造的。
10ስለዚህ ሴት ከመላእክት የተነሣ በራስዋ ሥልጣን ሊኖራት ይገባል።
10因此,為天使的緣故,女人應當在頭上有服權柄的記號。
11ነገር ግን በጌታ ዘንድ ሴት ያለ ወንድ ወንድም ያለ ሴት አይሆንም።
11然而在主裡面,女人不可以沒有男人,男人也不可以沒有女人。
12ሴት ከወንድ እንደ ሆነች እንዲሁ ወንድ ደግሞ በሴት ነውና፤ ሁሉም ከእግዚአብሔር ነው።
12因為正如女人是由男人而出,照樣,男人是藉著女人而生;萬有都是出於 神。
13በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?
13你們自己判斷一下,女人向 神禱告的時候不蒙頭,是合適的嗎?
14ወንድ ጠጉሩን ቢያስረዝም ነውር እንዲሆንበት፥ ሴት ግን ጠጉርዋን ብታስረዝም ክብር እንዲሆንላት ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን? ጠጉርዋ መጎናጸፊያ ሊሆን ተሰጥቶአታልና።
14人的本性不是也教導你們,如果男人有長頭髮,就是他的羞恥嗎?
16ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ፥ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም።
15如果女人有長頭髮,不就是她的榮耀嗎?因為頭髮是給她作蓋頭的。
17ነገር ግን በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለሚከፋ እንጂ ለሚሻል ስላልሆነ ይህን ትእዛዝ ስሰጥ የማመሰግናችሁ አይደለም።
16如果有人想要強辯,我們卻沒有這種習慣, 神的眾教會也沒有。
18በመጀመሪያ ወደ ማኅበር ስትሰበሰቡ በመካከላችሁ መለያየት እንዳለ እሰማለሁና፥ በአንድ በኩልም አምናለሁ።
17要用合適的態度吃主的聖餐(太26:26~28;可14:22~24;路22:17~20)我現在要吩咐你們,不是要稱讚你們,因為你們聚集在一起,並沒有得到益處,反而有害處。
19በእናንተ ዘንድ የተፈተኑት እንዲገለጡ በመካከላችሁ ወገኖች ደግሞ ሊሆኑ ግድ ነውና።
18首先,我聽說你們在聚會的時候,你們中間起了分裂,這話我也稍微相信。
20እንግዲህ አብራችሁ ስትሰበሰቡ የምትበሉት የጌታ እራት አይደለም፤
19你們中間會有分黨結派的事,這是必然的,為的是要使那些經得起考驗的人顯明出來。
21በመብላት ጊዜ እያንዳንዱ የራሱን እራት ይበላልና፥ አንዱም ይራባል አንዱ ግን ይሰክራል።
20你們聚集在一起,不是吃主的晚餐,
22የምትበሉባቸውና የምትጠጡባቸው ቤቶች የላችሁምን? ወይስ የእግዚአብሔርን ማኅበር ትንቃላችሁን አንዳችም የሌላቸውን ታሳፍራላችሁን? ምን ልበላችሁ? በዚህ ነገር ላመስግናችሁን? አላመሰግናችሁም።
21因為吃的時候,各人都先吃自己的晚餐,結果有人飢餓,有人醉了。
23ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠሁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለሁና፤
22難道你們沒有家可以吃喝嗎?還是你們藐視 神的教會,使那些沒有的羞愧呢?我向你們可以說甚麼呢?稱讚你們嗎?在這事上我不能稱讚。
24ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም። እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
23我當日傳交給你們的,原是從主領受的,就是主耶穌被出賣的那一夜,他拿起餅來,
25እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ። ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
24祝謝了,就擘開,說:“這是我的身體,為你們擘開的;你們應當這樣行,為的是記念我。”
26ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና።
25飯後,照樣拿起杯來,說:“這杯是用我的血所立的新約,你們每逢喝的時候,應當這樣行,為的是記念我。”
27ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት።
26你們每逢吃這餅,喝這杯,就是宣揚主的死,直等到他來。
28ሰው ግን ራሱን ይፈትን፥ እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤
27因此,無論甚麼人若用不合適的態度吃主的餅,喝主的杯,就是得罪主的身體、主的血了。
29ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና።
28所以人應當省察自己,然後才吃這餅,喝這杯。
30ስለዚህ በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል።
29因為那吃喝的人,如果不辨明是主的身體,就是吃喝定在自己的身上的罪了。
31ራሳችንን ብንመረምር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤
30因此,你們中間有許多人是軟弱的,患病的,而且死了的也不少。
32ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።
31我們若仔細省察自己,就不會受審判了。
33ስለዚህ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ ለመብላት በተሰበሰባችሁ ጊዜ እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ።
32然而我們被主審判的時候,是受他的管教,免得和世人一同被定罪。
34ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ። የቀረውንም ነገር በመጣሁ ጊዜ እደነግጋለሁ።
33所以,我的弟兄們,你們聚集在一起吃的時候,要彼此等待。
34如果有人餓了,就應當在家裡先吃,免得你們聚集在一起的時候受到審判。其餘的事,我來的時候再作安排。