Amharic: New Testament

聖經新譯本

Luke

21

1ዓይኑንም አንሥቶ መባቸውን በመዝገብ የሚጥሉ ባለ ጠጎችን አየ።
1窮寡婦的奉獻(可12:41~44)耶穌抬眼看見有錢的人把奉獻投入奉獻箱。
2አንዲትም ድሀ መበለት ሁለት ሳንቲም በዚያ ስትጥል አየና።
2他又看見一個窮寡婦,投入兩個小錢,
3እውነት እላችኋለሁ፥ ይህች ድሀ መበለት ከሁሉ ይልቅ አብልጣ ጣለች፤
3就說:“我實在告訴你們,這個窮寡婦所投的,比眾人投的更多。
4እነዚህ ሁሉ ከትርፋቸው ወደ እግዚአብሔር መዝገብ ጥለዋልና፤ ይህች ግን ከጕድለትዋ የነበራትን ትዳርዋን ሁሉ ጣለች አለ።
4因為這些人都是把自己剩餘的投進去作奉獻,這寡婦是自己不足,卻把所有養生的都投進去了。”
5አንዳንዶቹም ስለ መቅደስ በመልካም ድንጋይና በተሰጠው ሽልማት እንዳጌጠ ሲነጋገሩ። ይህማ የምታዩት ሁሉ፥
5預言聖殿被毀(太24:1~2;可13:1~2)有人在談論聖殿,是用美麗的石頭和供物裝飾的。耶穌說:
6ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ የማይቀርበት ዘመን ይመጣል አለ።
6“你們看見的這些,到了日子,必沒有一塊石頭留在另一塊石頭上面,每一塊都要拆下來。”
7እነርሱም። መምህር ሆይ፥ እንግዲህ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ይሆን ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ጠየቁት።
7這世代終結的預兆(太10:17~22,24:3~14;可13:3~13)那些人問他:“老師,甚麼時候會有這些事呢?這些事要發生的時候,有甚麼預兆呢?”
8እንዲህም አለ። እንዳትስቱ ተጠንቀቁ፤ ብዙዎች። እኔ ነኝ፥ ዘመኑም ቀርቦአል እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ እነርሱን ተከትላችሁ አትሂዱ።
8他說:“你們要小心,不要被人迷惑。因為有許多人要來,假冒我的名說:‘我就是基督’,又說:‘時候近了。’你們不要跟從這些人。
9ጦርንና ሁከትንም በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ አስቀድሞ ይሆን ዘንድ ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ወዲያው አይሆንም።
9你們要聽見戰亂和暴動,但不要驚慌,因為這些事是必先發生的,不過結局卻不會立刻就到。”
10በዚያን ጊዜ እንዲህ አላቸው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ፥ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣል፤
10過了一會兒,耶穌又對他們說:“一個民族要起來攻打另一個民族,一個國家要起來攻打另一個國家。
11ታላቅም የምድር መናወጥና በልዩ ልዩ ስፍራ ቸነፈር ራብም ይሆናል፤ የሚያስፈራም ነገር ከሰማይም ታላቅ ምልክት ይሆናል።
11到處必有大地震、饑荒和瘟疫,天上必有又恐怖又巨大的預兆。
12ከዚህም ሁሉ በፊት እጃቸውን በላያችሁ ይጭናሉ ያሳድዱአችሁማል፤ ስለ ስሜም ወደ ምኵራብና ወደ ወኅኒ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ወደ ነገሥታትና ወደ ገዥዎችም ይወስዱአችኋል፤
12但在這一切以先,人必為我的名,下手拘捕、迫害你們,把你們交給會堂,下在監裡,甚至押到君王和總督面前,
13ይህም ለምስክርነት ይሆንላችኋል።
13結果卻成了你們見證的機會。
14ሰለዚህ እንዴት እንድትመልሱ አስቀድማችሁ እንዳታስቡ በልባችሁ አኑሩት፤
14所以,你們應當心裡鎮定,用不著預先思慮怎樣申辯。
15ወደረኞቻችሁ ሁሉ ሊቃወሙና ሊከራከሩ የማይችሉትን አፍና ጥበብ እሰጣችኋለሁና።
15因為我必賜給你們口才、智慧,是你們所有的敵人不能抵抗,也不能駁倒的。
16ወላጆችም ስንኳ ወንድሞችም ዘመዶችም ወዳጆችም አሳልፈው ይሰጡአችኋል፥ ከእናንተም አንዳንዱን ይገድላሉ፤
16你們也會被父母、弟兄、親戚、朋友出賣,他們又要害死你們一些人。
17በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
17你們要因我的名,被眾人恨惡,
18ከራሳችሁም አንዲት ጠጉር ስንኳ አትጠፋም፤
18然而連你們的一根頭髮,也必不失落。
19በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ።
19你們要以堅忍的心志,贏取自己的靈魂。
20ኢየሩሳሌም ግን በጭፍራ ተከባ ስታዩ በዚያን ጊዜ ጥፋትዋ እንደ ቀረበ እወቁ።
20預言耶路撒冷被毀(太24:15~21;可13:14~19)“當你們看見耶路撒冷被軍隊圍困的時候,就知道它荒涼的日子近了。
21የዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥ በመካከልዋም ያሉ ከእርስዋ ፈቀቅ ይበሉ፥ በገጠር ያሉም ወደ እርስዋ አይግቡ፤
21那時,住在猶太的,應該逃到山上;住在城裡的,要離開;住在鄉下的,不要進城。
22የተጻፈው ሁሉ እንዲፈጸም ይህ የበቀል ጊዜ ነውና።
22因為這是報仇的日子,使經上的一切話都得應驗。
23በዚያን ወራት ለእርጕዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው፤ ታላቅ ችግር በምድር ላይ፥ በዚህም ሕዝብ ላይ ቍጣ ይሆናልና፤
23當那些日子,懷孕的和乳養孩子的有禍了!因為大災難要臨到這地,烈怒要臨到這民。
24በሰይፍ ስለትም ይወድቃሉ፤ ወደ አሕዛብ ሁሉም ይማረካሉ፤ የአሕዛብም ዘመን እስኪፈጸም ድረስ ኢየሩሳሌም በአሕዛብ የተረገጠች ትሆናለች።
24他們將倒在刀下,被擄到各國,耶路撒冷必被外族人踐踏,直到外族人的日期滿足。
25በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ከባሕሩና ከሞገዱም ድምፅ የተነሣ እያመነቱ ይጨነቃሉ፤
25人子必駕雲降臨(太24:29~35;可13:24~31)“日月星辰將有異兆;在地上,各國也要因著海洋波濤的咆哮而困苦不安。
26ሰዎችም ከፍርሃትና በዓለም የሚመጣበትን ከመጠበቅ የተነሣ ይደክማሉ፤ የሰማያት ኃይላት ይናወጣሉና።
26天上的萬象震動,人因為等待即將臨到世界的事,都嚇昏了。
27በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በኃይልና በብዙ ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል።
27那時,他們要看見人子,帶著能力,滿有榮耀,駕著雲降臨。
28ይህም ሊሆን ሲጀምር ቤዛችሁ ቀርቦአልና አሻቅባችሁ ራሳችሁን አንሡ።
28一有這些事,你們就當挺身昂首,因為你們的救贖近了。”
29ምሳሌንም ነገራቸው እንዲህ ሲል። በለስንና ዛፎችን ሁሉ እዩ፤
29耶穌又給他們講了一個比喻:“你們看看無花果樹和各樣的樹。
30ሲያቈጠቍጡ ተመልክታችሁ በጋ አሁን እንደ ቀረበ ራሳችሁ ታውቃላችሁ።
30它們甚麼時候發芽,你們看見了,就知道夏天近了。
31እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህ ሁሉ መሆኑን ስታዩ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ ቀረበች እወቁ።
31同樣,你們甚麼時候看見這些事發生,也應該知道 神的國近了。
32እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።
32我實在告訴你們,這一切都必定發生,然後這世代才會過去。
33ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም።
33天地都過去,但我的話決不會廢去。
34ነገር ግን ልባችሁ በመጠጥ ብዛትና በስካር ስለ ትዳርም በማሰብ እንዳይከብድ፥ ያ ቀንም በድንገት እንዳይመጣባችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤
34警醒祈求“你們應當自己小心,免得在貪食醉酒和生活的掛慮壓住你們的心的時候,那日子突然臨到你們,
35በምድር ሁሉ ላይ በሚቀመጡ ሁሉ እንደ ወጥመድ ይደርስባቸዋልና።
35正如網羅臨到全地的所有居民。
36እንግዲህ ሊመጣ ካለው ከዚህ ሁሉ ለማምለጥ፥ በሰው ልጅም ፊት ለመቆም እንድትችሉ ስትጸልዩ ሁል ጊዜ ትጉ።
36你們要時刻警醒,常常祈求,好讓你們能逃避這一切要發生的事,可以站在人子面前。”
37ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር።
37耶穌白天在殿裡教導人,晚上就到橄欖山上去過夜。
38ሕዝቡም ሁሉ ይሰሙት ዘንድ ማልደው በመቅደስ ወደ እርሱ ይመጡ ነበር።
38群眾清早起來上聖殿,到他那裡要聽他講道。