1ኢየሱስም እነዚህን ቃሎች ሁሉ በፈጸመ ጊዜ፥
1商議怎樣殺害耶穌(可14:1~2;路22:1~2)耶穌說完了這一切話,就對門徒說:
2ለደቀ መዛሙርቱ። ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንዲሆን ታውቃላችሁ፥ የሰው ልጅም ሊሰቀል አልፎ ይሰጣል አለ።
2“你們知道兩天之後就是逾越節,人子將要被交給人,釘在十字架上。”
3በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ፥
3那時,祭司長和民間的長老聚集在大祭司該亞法的官邸,
4ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ፤
4商議怎樣用詭計逮捕耶穌,把他殺害。
5ነገር ግን። በሕዝቡ ዘንድ ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ።
5不過他們說:“不可在節期下手,免得引起民眾暴動。”
6ኢየሱስም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ፥
6有女人用香膏膏主(可14:3~9;約12:1~8)耶穌在伯大尼,在患痲風的西門家裡的時候,
7አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የበዛ ሽቱ የሞላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ እርሱ ቀረበች በማዕድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችው።
7有一個女人拿著一瓶珍貴的香膏,前來把它澆在耶穌的頭上。
8ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው ተቈጡና። ይህ ጥፋት ለምንድር ነው?
8門徒看見了,就很生氣,說:“為甚麼這樣浪費呢?
9ይህ በብዙ ዋጋ ተሽጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና አሉ።
9這香膏可以賣很多錢,賙濟窮人。”
10ኢየሱስም ይህን አውቆ እንዲህ አላቸው። መልካም ሥራ ሠርታልኛለችና ሴቲቱንስ ስለ ምን ታደክሙአታላችሁ?
10耶穌知道了,就說:“為甚麼難為這個女人呢?她為我作了一件美事。
11ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም፤
11你們常常有窮人跟你們在一起,然而卻不常有我。
12እርስዋ ይህን ሽቱ በሰውነቴ ላይ አፍስሳ ለመቃብሬ አደረገች።
12她把這香膏澆在我身上,是為了安葬我而作的。
13እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።
13我實在告訴你們,這福音無論傳到世界上甚麼地方,這女人所作的都要傳講,來記念她。”
14በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ።
14猶大出賣耶穌(可14:10~11;路22:3~6)那時,十二門徒中的一個,就是加略人猶大,去見祭司長,說:
15ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ? እነርሱም ሠላሳ ብር መዘኑለት።
15“如果我把他交給你們,你們願意給我甚麼呢?”他們就給了他三十塊銀子。
16ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር።
16從那時起,他就找機會把耶穌交給他們。
17በቂጣው በዓል በመጀመሪያ ቀን ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው። ፋሲካን ትበላ ዘንድ ወዴት ልናሰናዳልህ ትወዳለህ አሉት።
17最後的晚餐(可14:12~26;路22:7~23;約13:21~30)除酵節的第一天,門徒前來問耶穌:“你要我們在哪裡為你預備逾越節的晚餐呢?”
18እርሱም። ወደ ከተማ ከእገሌ ዘንድ ሄዳችሁ። መምህር። ጊዜዬ ቀርቦአል፤ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ከአንተ ዘንድ ፋሲካን አደርጋለሁ ይላል በሉት አለ።
18他說:“你們到城裡去見某人,對他說,老師說:‘我的時候快到了;我要到你那裡和我的門徒守逾越節。’”
19ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ እንዳዘዛቸው አደረጉ ፋሲካንም አሰናዱ።
19門徒照耶穌的指示去作,預備好了逾越節的晚餐。
20በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
20到了晚上,耶穌和十二門徒一同吃晚餐。
21ሲበሉም። እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ እኔን አሳልፎ ይሰጣል አለ።
21他們吃的時候,耶穌說:“我實在告訴你們,你們中間有一個人要出賣我。”
22እጅግም አዝነው እያንዳንዱ። ጌታ ሆይ፥ እኔ እሆንን? ይሉት ጀመር።
22他們就很憂愁,一個一個地問他:“主啊,是我嗎?”
23እርሱም መልሶ። ከእኔ ጋር እጁን በወጭቱ ያጠለቀ፥ እኔን አሳልፎ የሚሰጥ እርሱ ነው።
23他回答:“那和我一同把手蘸在盤子裡的人,他要出賣我。
24የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይሄዳል፥ ነገር ግን የሰው ልጅ አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት፤ ያ ሰው ባልተወለደ ይሻለው ነበር አለ።
24正如經上指著人子所說的,他固然要離世,但出賣人子的那人有禍了!他沒有生下來倒好。”
25አሳልፎ የሚሰጠው ይሁዳም መልሶ። መምህር ሆይ፥ እኔ እሆንን? አለ፤ አንተ አልህ አለው።
25那出賣耶穌的猶大說:“拉比,是我嗎?”他說:“這是你說的。”
26ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና። እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው አለ።
26他們吃的時候,耶穌拿起餅來,祝謝了就擘開,遞給門徒,說:“你們拿去吃吧,這是我的身體。”
27ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ። ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤
27耶穌又拿起杯來,祝謝了就遞給他們,說:“你們都喝吧,
28ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው።
28這是我的血,是為立約的,為許多人流出來,使罪得赦。
29ነገር ግን እላችኋለሁ፥ በአባቴ መንግሥት ከእናንተ ጋር ከዚህ ከወይን ፍሬ አዲሱን እስከምጠጣበት እስከዚያ ቀን ድረስ ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣውም።
29我告訴你們,從今以後我必不再喝這葡萄酒,直到我和你們在我父的國裡喝新酒的那一天。”
30መዝሙርም ከዘመሩ በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ወጡ።
30他們唱完了詩,就出來往橄欖山去。
31በዚያን ጊዜ ኢየሱስ። በዚች ሌሊት ሁላችሁ በእኔ ትሰናከላላችሁ፤ እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና፤
31預言彼得不認主(可14:27~31;路22:31~34;約13:36~38)那時,耶穌對他們說:“今天晚上,你們因我的緣故都要後退,因為經上記著:‘我要擊打牧人,羊群就分散了。’
32ከተነሣሁ በኋላ ግን ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው።
32我復活以後,要比你們先到加利利去。”
33ጴጥሮስም መልሶ። ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም አለው።
33彼得對他說:“就算所有的人都因你的緣故後退,我卻永不後退。”
34ኢየሱስ። እውነት እልሃለሁ፥ በዚች ሌሊት ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው።
34耶穌對他說:“我實在告訴你,今天晚上雞叫以前,你會三次不認我。”
35ጴጥሮስ። ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን፥ ከቶ አልክድህም አለው። ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ደግሞ እንደዚሁ አሉ።
35彼得對他說:“就算必須與你一同死,我也決不會不認你。”門徒也都這樣說。
36በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ከእነርሱ ጋር ጌቴሴማኒ ወደምትባል ስፍራ መጣ ደቀ መዛሙርቱንም። ወዲያ ሄጄ ስጸልይ ሳለ በዚህ ተቀመጡ አላቸው።
36在客西馬尼禱告(可14:32~42;路22:39~46)耶穌和門徒來到一個地方,名叫客西馬尼,就對門徒說:“你們坐在這裡,我要到那邊去禱告。”
37ጴጥሮስንም ሁለቱንም የዘብዴዎስን ልጆች ወስዶ ሊያዝን ሊተክዝም ጀመር።
37他帶了彼得和西庇太的兩個兒子一起去,心裡憂愁難過,
38ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ አዘነች፤ በዚህ ቆዩ ከእኔም ጋር ትጉ አላቸው።
38對他們說:“我的心靈痛苦得快要死了;你們留在這裡,與我一同警醒吧。”
39ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀና ሲጸልይ። አባቴ፥ ቢቻልስ፥ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ፤ ነገር ግን አንተ እንደምትወድ ይሁን እንጂ እኔ እንደምወድ አይሁን አለ።
39他稍往前走,把臉俯伏在地上,禱告說:“我的父啊!可能的話,求你使這杯離開我;但不要照我的意思,只要照你的旨意。”
40ወደ ደቀ መዛሙርቱም መጣ፤ ተኝተውም አገኛቸውና ጴጥሮስን። እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን?
40耶穌回到門徒那裡,看見他們都睡著了,就對彼得說:“你們連一個小時也不能同我警醒嗎?
41ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።
41應當警醒、禱告,免得陷入試探;你們心靈雖然願意,肉體卻是軟弱的。”
42ደግሞ ሁለተኛ ሄዶ ጸለየና። አባቴ፥ ይህች ጽዋ ሳልጠጣት ታልፍ ዘንድ የማይቻል እንደ ሆነ፥ ፈቃድህ ትሁን አለ።
42他又再次走開,禱告說:“我的父啊!如果這杯不能離開我,一定要我喝,就願你的旨意成全。”
43ደግሞም መጥቶ ዓይኖቻቸው በእንቅልፍ ከብደው ነበርና ተኝተው አገኛቸው።
43他再回來的時候,看見門徒睡著了,因為他們十分疲倦。
44ደግሞም ትቶአቸው ሄደ፥ ሦስተኛም ያንኑ ቃል ደግሞ ጸለየ።
44他又離開他們,第三次去禱告,說的也是同樣的話。
45ከዚያ ወዲያ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጥቶ። እንግዲህስ ተኙ ዕረፉም፤ እነሆ፥ ሰዓቲቱ ቀርባለች የሰው ልጅም በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል።
45然後,他回到門徒那裡,對他們說:“你們還在睡覺休息嗎?看哪,時候到了,人子要被交在罪人的手裡了。
46ተነሡ፥ እንሂድ፤ እነሆ፥ አሳልፎ የሚሰጠኝ ቀርቦአል አላቸው።
46起來,我們走吧!出賣我的人來了。”
47ይህንም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ መጣ፥ ከእርሱም ጋር ብዙ ሕዝብ ሰይፍና ጐመድ ይዘው ከካህናት አለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሎች ዘንድ መጡ።
47耶穌被捕(可14:43~50;路22:47~53;約18:3~11)耶穌還在說話的時候,十二門徒中的猶大,帶著一大群拿著刀棒的人來到,他們是祭司長和民間的長老派來的。
48አሳልፎ የሚሰጠውም። የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት ብሎ ምልክት ሰጥቶአቸው ነበር።
48出賣耶穌的人給他們一個暗號,說:“我跟誰親嘴,誰就是他;你們可以抓住他。”
49ወዲያውም ወደ ኢየሱስ ቀረበና። መምህር ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ብሎ ሳመው።
49他立刻前來對耶穌說:“拉比,你好。”跟著就與他親嘴。
50ኢየሱስም። ወዳጄ ሆይ፥ ለምን ነገር መጣህ? አለው። በዚያን ጊዜ ቀረቡ እጃቸውንም በኢየሱስ ላይ ጭነው ያዙት።
50耶穌對他說:“朋友,你來要作的事,快作吧!”於是那些人上前來,動手拿住耶穌,逮捕了他。
51እነሆም፥ ከኢየሱስ ጋር ከነበሩት አንዱ እጁን ዘርግቶ ሰይፉን መዘዘና የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መትቶ ጆሮውን ቈረጠው።
51有一個與耶穌在一起的人,伸手拔出刀來,砍了大祭司的僕人一刀,削掉他的一隻耳朵。
52በዚያን ጊዜ ኢየሱስ እንዲህ አለው። ሰይፍ የሚያነሡ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉና ሰይፍህን ወደ ስፍራው መልስ።
52耶穌對他說:“把你的刀收回原處!凡動刀的必死在刀下。
53ወይስ አባቴን እንድለምን እርሱም አሁን ከአሥራ ሁለት ጭፍሮች የሚበዙ መላእክት እንዲሰድልኝ የማይቻል ይመስልሃልን?
53你以為我不能求我的父,他就馬上給我派十二營以上的天使下來嗎?
54እንዲህ ከሆነስ። እንደዚህ ሊሆን ይገባል የሚሉ መጻሕፍት እንዴት ይፈጸማሉ?
54如果這樣,經上預言這事必須發生,怎能應驗呢?”
55በዚያን ሰዓት ኢየሱስ ለሕዝቡ። ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ልትይዙኝ ወጣችሁን? በመቅደስ ዕለት ዕለት እያስተማርሁ ከእናንተ ጋር ስቀመጥ ሳለሁ አልያዛችሁኝም።
55那時,耶穌對眾人說:“你們帶著刀棒出來,把我當作強盜捉拿嗎?我天天坐在殿裡教導人,你們卻沒有逮捕我。
56ነገር ግን ይህ ሁሉ የሆነ የነቢያት መጻሕፍት ይፈጸሙ ዘንድ ነው አለ። በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ትተውት ሸሹ።
56但這整件事的發生,是要應驗先知書上的話。”那時,門徒都離開他逃跑了。
57ኢየሱስን የያዙትም ጻፎችና ሽማግሎች ወደ ተከማቹበት ወደ ሊቀ ካህናቱ ወደ ቀያፋ ወሰዱት።
57大祭司審問耶穌(可14:53~65;路22:54、66~71;約18:12~13、19~24)那些逮捕了耶穌的人,把他押去見大祭司該亞法。那時經學家和長老已經聚集在那裡了。
58ጴጥሮስ ግን እስከ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ድረስ ሩቅ ሆኖ ተከተለው፥ የነገሩንም ፍጻሜ ያይ ዘንድ ወደ ውስጥ ገብቶ ከሎሌዎቹ ጋር ተቀመጠ።
58彼得遠遠地跟著耶穌,直到大祭司的官邸。他進到裡面,和差役坐在一起,要看事情怎樣了結。
59የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ሸንጐውም ሁሉ እንዲገድሉት በኢየሱስ ላይ የሐሰት ምስክር ይፈልጉ ነበር፥ አላገኙም፤
59祭司長和公議會全體都想找假證供來控告耶穌,好把他處死;
60ብዙም የሐሰት ምስክሮች ምንም ቢቀርቡ አላገኙም።
60雖然有許多人前來作假證供,卻找不著證據。最後有兩個人前來說:
61በኋላም ሁለት ቀርበው። ይህ ሰው። የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ አፍርሼ በሦስት ቀን ልሠራው እችላለሁ ብሎአል አሉ።
61“這人說過:‘我可以拆毀 神的聖所,三日之內又把它建造起來。’”
62ሊቀ ካህናቱም ተነሥቶ። እነዚህ ለሚመሰክሩብህ አንድ ስንኳ አትመልስምን? አለው።
62大祭司就站起來,對耶穌說:“你為甚麼不回答?這些人作證,控告你的是甚麼呢?”
63ኢየሱስ ግን ዝም አለ። ሊቀ ካህናቱም። አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ የሆንህ እንደ ሆነ እንድትነግረን በሕያው እግዚአብሔር አምልሃለሁ አለው።
63耶穌卻不作聲。大祭司又對他說:“我指著永生的 神要你起誓,告訴我們你是不是基督、 神的兒子。”
64ኢየሱስም። አንተ አልህ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከእንግዲህ ወዲህ የሰው ልጅ በኃይል ቀኝ ሲቀመጥ በሰማይም ደመና ሲመጣ ታያላችሁ አለው።
64耶穌回答:“這是你說的;但我告訴你們:從今以後,你們要看見人子,坐在權能者的右邊,駕著天上的雲降臨。”
65በዚያን ጊዜ ሊቀ ካህናቱ ልብሱን ቀዶ። ተሳድቦአል እንግዲህ ወዲህ ምስክሮች ስለ ምን ያስፈልገናል? እነሆ፥ ስድቡን አሁን ሰምታችኋል፤ ምን ይመስላችኋል? አለ።
65大祭司就撕開衣服,說:“他說了褻瀆的話,我們還要甚麼證人呢?你們現在聽見了這褻瀆的話,
66እነርሱም። ሞት ይገባዋል ብለው መለሱ።
66認為怎樣呢?”他們回答:“他是該死的。”
67በዚያን ጊዜ በፊቱ ተፉበት፤ ጐሰሙትም፥ ሌሎችም በጥፊ መትተው። ክርስቶስ ሆይ፥ በጥፊ የመታህ ማን ነው?
67於是他們吐唾沫在他的臉上,用拳頭打他,也有人用掌摑他,說:
68ትንቢት ተናገርልን አሉ።
68“基督啊,向我們說預言吧!是誰打你呢?”
69ጴጥሮስም ከቤት ውጭ በአጥሩ ግቢ ተቀምጦ ነበር፤ አንዲት ገረድም ወደ እርሱ ቀርባ። አንተ ደግሞ ከገሊላው ከኢየሱስ ጋር ነበርህ አለችው።
69彼得三次不認主(可14:66~72;路22:55~62;約18:16~18、25~27)彼得坐在外面的院子裡,有一個婢女走過來對他說:“你也是和加利利人耶穌一夥的。”
70እርሱ ግን። የምትዪውን አላውቀውም ብሎ በሁሉ ፊት ካደ።
70彼得卻當眾否認,說:“我不知道你說甚麼。”
71ወደ በሩም ሲወጣ ሌላይቱ አየችውና በዚያ ላሉት። ይህ ደግሞ ከናዝሬቱ ከኢየሱስ ጋር ነበረ አለች።
71他出到門口,又有一個婢女看見他,就對那裡的人說:“這人是和拿撒勒人耶穌一夥的。”
72ዳግመኛም ሲምል። ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ካደ።
72彼得再次否認,並且發誓說:“我不認識那個人。”
73ጥቂትም ቈይተው በዚያ ቆመው የነበሩ ቀርበው ጴጥሮስን። አነጋገርህ ይገልጥሃልና በእውነት አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አሉት።
73過了一會,站在那裡的人前來對他說:“你的確是他們中間的一個,因為一聽你的口音就認出來了。”
74በዚያን ጊዜ። ሰውየውን አላውቀውም ብሎ ሊራገምና ሊምል ጀመረ። ወዲያውም ዶሮ ጮኸ።
74彼得就發咒起誓說:“我不認識那一個人。”立刻雞就叫了。
75ጴጥሮስም። ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው የኢየሱስ ቃል ትዝ አለው፤ ወደ ውጭም ወጥቶ መራራ ልቅሶ አለቀሰ።
75彼得想起耶穌所說的話:“雞叫以前,你會三次不認我”,他就出去痛哭。