1Brāļi, es negribu atstāt jūs neziņā, ka mūsu tēvi visi bija zem padebess un visi gāja caur jūru,
1ወንድሞች ሆይ፥ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ። አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ ሁሉም በባሕር መካከል ተሻገሩ፤
2Un padebesī, un jūrā visi ir kristīti Mozū,
2ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመናና በባሕር ተጠመቁ፤
3Un visi ēda to pašu garīgo barību,
3ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ፤
4Un visi dzēra to pašu garīgo dzērienu (viņi dzēra no garīgās klints, kas tiem sekoja), bet klints bija Kristus;
4ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ ዓለት ጠጥተዋልና፥ ያም ዓለት ክርስቶስ ነበረ።
5Tomēr daudzi no viņiem Dievam nepatika; un viņi gāja bojā tuksnesī.
5እግዚአብሔር ግን ከእነርሱ በሚበዙት ደስ አላለውም፥ በምድረ በዳ ወድቀዋልና።
6Bet tas viss notika mums par brīdinājumu, lai mēs nekārotu pēc ļauna, kā viņi ir kārojuši;
6እነዚህም ክፉ ነገር እንደ ተመኙ እኛ ደግሞ እንዳንመኝ ይህ ምሳሌ ሆነልን።
7Un netopiet elku kalpi kā daži no viņiem, kā ir rakstīts: Šī tauta apsēdās, lai ēstu un dzertu, un piecēlās, lai dejotu. (2.Moz.32,6)
7ሕዝብም ሊበሉ ሊጠጡም ተቀመጡ ሊዘፍኑም ተነሡ ተብሎ እንደ ተጻፈ ከእነርሱ አንዳንዶቹ እንዳደረጉት ጣዖትን የምታመልኩ አትሁኑ።
8Un nenodosimies netiklībai, kā daži no viņiem bija nodevušies, un vienā dienā krita divdesmit trīs tūkstoši.
8ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንደ ሴሰኑ በአንድ ቀንም ሁለት እልፍ ከሦስት ሺህ እንደ ወደቁ አንሴስን።
9Un nekārdināsim Kristu, kā daži no tiem kārdinājuši, un viņi gāja bojā no čūskām.
9ከእነርሱም አንዳንዶቹ ጌታን እንደ ተፈታተኑት በእባቦቹም እንደ ጠፉ ጌታን አንፈታተን።
10Un nekurniet, kā daži no tiem kurnējuši un gāja bojā no postītāja.
10ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደ ጠፉ አታንጐርጕሩ።
11Tas viss viņiem noticis mācībai, bet mums, kas dzīvojam pēdējos mūžos, tas uzrakstīts brīdinājumam.
11ይህም ሁሉ እንደ ምሳሌ ሆነባቸው፥ እኛንም የዘመናት መጨረሻ የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ።
12Tātad, kas sevī iedomājas, ka viņš stāv, lai pielūko, ka nekrīt!
12ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።
13Kārdinājumi lai jums neuzbrūk, izņemot cilvēcīgos! Bet Dievs ir uzticīgs. Viņš neļaus jūs kārdināt pāri jūsu spējām, bet reizē ar kārdinājumu dos izturību, lai jūs varētu pastāvēt.
13ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።
14Tāpec, mani mīļie, bēdziet no kalpošanas elkiem!
14ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ።
15Es runāju kā saprātīgiem. Jūs paši apsveriet, ko es saku!
15ልባሞች እንደ መሆናችሁ እላለሁ፤ በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ።
16Svētības biķeris, ko svētījam, vai tas nav savienošanās ar Kristus asinīm? Un maize, ko laužam, vai tā nav kopība ar Kunga miesu?
16የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን?
17Kā viena maize, tā mēs daudzi esam viena miesa, visi, kas ir šīs vienas maizes līdzdalībnieki.
17አንድ እንጀራ ስለ ሆነ፥ እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን፤ ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና።
18Skatiet Izraēli pēc miesas: vai tie, kas ēd upurdāvanas, neņem līdzdalību pie altāra?
18በሥጋ የሆነውን እስራኤል ተመልከቱ፤ መሥዋዕቱን የሚበሉ የመሠዊያው ማኅበረተኞች አይደሉምን?
19Vai tad es saku, ka elkupuris kas ir, vai ka elki kas ir?
19እንግዲህ ምን እላለሁ? ለጣዖት የተሠዋ ምናምን ነው እላለሁን? ወይስ ጣዖት ምናምን እንዲሆን እላለሁን?
20Bet ko pagāni upurē, to viņi upurē ļaunajiem gariem, bet ne Dievam. Bet es negribu, ka jūs būtu ļauno garu līdzdalībnieki.
20አይደለም፤ ነገር ግን አሕዛብ የሚሠዉት ለአጋንንት እንዲሆን እንጂ ለእግዚአብሔር እንዳይሠዉ እላለሁ፤ ከአጋንንትም ጋር ማኅበረተኞች እንድትሆኑ አልወድም።
21Jūs nevarat būt Kunga galda un ļauno garu galda dalībnieki.
21የጌታን ጽዋና የአጋንንትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፤ ከጌታ ማዕድና ከአጋንንት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም።
22Vai mēs lai izaicinām Kungu? Vai mēs esam varenāki par Viņu? Viss man ir atļauts, bet ne viss ir noderīgs.
22ወይስ ጌታን እናስቀናውን? እኛስ ከእርሱ ይልቅ እንበረታለንን?
23Viss man ir atļauts, bet ne viss ceļ.
23ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።
24Neviens lai nemeklē savu, bet cita labumu!
24እያንዳንዱ የባልንጀራውን ጥቅም እንጂ አንድ ስንኳ የራሱን ጥቅም አይፈልግ።
25Visu, ko pārdod gaļas tirgū, ēdiet, nekā nejautādami sirdsapziņas dēļ!
25በሥጋ ገበያ የሚሸጠውን ሁሉ ከሕሊና የተነሣ ሳትመራመሩ ብሉ፤
26Kungam pieder zeme un tās pārpilnība. (Ps 23,1)
26ምድርና በእርስዋ የሞላባት ሁሉ የጌታ ነውና።
27Ja kāds no neticīgajiem jūs aicina un jūs gribat iet, tad ēdiet visu, ko ceļ jums priekšā, nekā netaujādami sirdsapziņas dēļ!
27ከማያምኑ ሰዎች አንዱም ቢጠራችሁ ልትሄዱም ብትወዱ ከሕሊና የተነሣ ሳትመራመሩ የሚያቀርቡላችሁን ሁሉ ብሉ።
28Bet ja kāds jums sacītu: Tas tika upurēts elkiem, tad neēdiet tā dēļ, kas jums aizrādīja, un sirdsapziņas dēļ.
28ማንም ግን። ይህ ለጣዖት የተሠዋ ነው ቢላችሁ ከዚያ ካስታወቃችሁና ከሕሊና የተነሣ አትብሉ፤
29Tomēr es nedomāju tavu, bet tā otra sirdsapziņu. Jo kāpēc lai sveša sirdsapziņa spriestu tiesu par manu brīvību?
29ስለ ባልንጀራህ ሕሊና እንጂ ስለ ገዛ ሕሊናህ አልናገርም። አርነቴ በሌላ ሰው ሕሊና የሚፈርድ Avረ ስለ ምንድር ነው?
30Ja es pateikdamies piedalos, kāpēc tad tieku zaimots par to, par ko es pateicos?
30እኔም በጸጋ ብበላ፥ በነገሩ ስለማመሰግንበት ስለ ምን እሰደባለሁ?
31Tātad, vai jūs ēdat, vai dzerat, vai citu ko darāt, visu dariet Dieva godam!
31እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።
32Neesiet piedauzība ne jūdiem, ne pagāniem, ne Dieva Baznīcai,
32እኔ ደግሞ ብዙዎቹ ይድኑ ዘንድ ለጥቅማቸው እንጂ የራሴን ጥቅም ሳልፈልግ በሁሉ ነገር ሰውን ሁሉ ደስ እንደማሰኝ፥ ለአይሁድም ለግሪክም ሰዎች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንም ማሰናከያ አትሁኑ።
33Tā kā arī es visiem visumā esmu tīkams, nemeklēdams savu, bet daudzu labumu, lai tie tiktu izglābti.