1Esiet sekotāji man kā es Kristum!
1እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።
2Brāļi, par to es jūs cildinu, ka jūs visur mani pieminat un pildāt manas pavēles tā, kā es jums tās esmu devis.
2ወንድሞች ሆይ፥ በሁሉ ስለምታስቡኝና አሳልፌ እንደ ሰጠኋችሁ ወግን ፈጽማችሁ ስለ ያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ።
3Bet es gribu, lai jūs zinātu, ka katra vīra galva ir Kristus, bet sievas galva ir vīrs, un Kristus galva ir Dievs.
3ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ።
4Katrs vīrietis, kas, apsedzis galvu, lūdz Dievu vai pravieto, dara negodu savai galvai.
4ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ ሁሉ ራሱን ያዋርዳል።
5Bet katra sieviete, kas lūdz Dievu vai pravieto ar neapsegtu galvu, dara negodu savai gadvai, jo tā ir tāpat kā apcirpta.
5ራስዋን ሳትሸፍን ግን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራስዋን ታዋርዳለች፤ እንደ ተላጨች ያህል አንድ ነውና።
6Ja sieviete neaizsedzas, tad lai viņai nocērp matus! Tā kā sievietei ir kauns būt apcirptai vai noskūtai, tad lai apsedz galvu!
6ሴትም ራስዋን ባትሸፍን ጠጉርዋን ደግሞ ትቆረጥ፤ ለሴት ግን ጠጉርዋን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ ራስዋን ትሸፍን።
7Vīrietim nevajag galvu apsegt, jo viņš ir Dieva attēls un godība, bet sieviete ir vīra gods.
7ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት።
8Jo vīrietis nav no sievietes, bet sieviete no vīrieša; (1.Moz.2,21-22)
8ሴት ከወንድ ናት እንጂ ወንድ ከሴት አይደለምና።
9Arī vīrietis nav radīts sievietes dēļ, bet sieviete - vīrieša dēļ. (1.Moz.2,18 u.c.)
9ሴት ስለ ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ ስለ ሴት አልተፈጠረምና።
10Tāpēc sievietei galvā jānēsā varas zīme eņģeļu dēļ.
10ስለዚህ ሴት ከመላእክት የተነሣ በራስዋ ሥልጣን ሊኖራት ይገባል።
11Tomēr Kungā nav vīrietis bez sievietes, nedz sieviete bez vīrieša;
11ነገር ግን በጌታ ዘንድ ሴት ያለ ወንድ ወንድም ያለ ሴት አይሆንም።
12Jo kā sieviete no vīrieša, tā arī vīrietis no sievietes, bet viss no Dieva.
12ሴት ከወንድ እንደ ሆነች እንዲሁ ወንድ ደግሞ በሴት ነውና፤ ሁሉም ከእግዚአብሔር ነው።
13Spriediet jūs paši: vai pieklājas sievietei neaizsegtai Dievu lūgt?
13በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?
14Vai pati daba nemāca: ja kāds vīrietis audzē matus, tas viņam ir negods;
14ወንድ ጠጉሩን ቢያስረዝም ነውር እንዲሆንበት፥ ሴት ግን ጠጉርዋን ብታስረዝም ክብር እንዲሆንላት ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን? ጠጉርዋ መጎናጸፊያ ሊሆን ተሰጥቶአታልና።
15Bet ja sieviete audzē matus, tas viņai ir gods, jo mati viņai doti par aizsegu.
16ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ፥ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም።
16Bet ja kāds gribētu ķildoties, tad ne pie mums, ne Dieva Baznīcā tāda ieraduma nav.
17ነገር ግን በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለሚከፋ እንጂ ለሚሻል ስላልሆነ ይህን ትእዛዝ ስሰጥ የማመሰግናችሁ አይደለም።
17Bet šo es aizrādu ne cildinādams, jo jūsu sanāksmes nenāk jums par labu, bet par ļaunu.
18በመጀመሪያ ወደ ማኅበር ስትሰበሰቡ በመካከላችሁ መለያየት እንዳለ እሰማለሁና፥ በአንድ በኩልም አምናለሁ።
18Vispirms es dzirdu, ka jūsu draudzes sanāksmēs notiekot šķelšanās, un daļēji es tam ticu;
19በእናንተ ዘንድ የተፈተኑት እንዲገለጡ በመካከላችሁ ወገኖች ደግሞ ሊሆኑ ግድ ነውና።
19Jo šķelšanām gan jābūt, lai kļūtu redzami tie, kas starp jums ir uzticami.
20እንግዲህ አብራችሁ ስትሰበሰቡ የምትበሉት የጌታ እራት አይደለም፤
20Kad jūs sanākat kopā, tad tas vairs nav Kunga vakarēdiena baudīšanai;
21በመብላት ጊዜ እያንዳንዱ የራሱን እራት ይበላልና፥ አንዱም ይራባል አንዱ ግን ይሰክራል።
21Jo katrs steidzas paņemt ēšanai savu ēdienu, un tā dažs paliek izsalcis, bet dažs piedzeras.
22የምትበሉባቸውና የምትጠጡባቸው ቤቶች የላችሁምን? ወይስ የእግዚአብሔርን ማኅበር ትንቃላችሁን አንዳችም የሌላቸውን ታሳፍራላችሁን? ምን ልበላችሁ? በዚህ ነገር ላመስግናችሁን? አላመሰግናችሁም።
22Vai jums nav māju, kur ēst un dzert? Vai jūs nicināt Dieva Baznīcu un apkaunojat tos, kam nekā nav? Ko lai jums saku? Vai lai cildinu? Šai ziņā es jūs necildinu.
23ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠሁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለሁና፤
23Jo no Kunga es saņēmu, ko arī jums atstāju, ka Kungs Jēzus tanī naktī, kad Viņš tika nodots, paņēma maizi,
24ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም። እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
24Un pateikdamies lauza un sacīja: Ņemiet un ēdiet, šī ir mana Miesa, kas par jums tiks atdota; to dariet manai piemiņai!
25እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ። ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
25Tāpat arī biķeri pēc vakarēdiena, sacīdams: Šis biķeris ir Jaunā derība manās Asinīs; to dariet, cikkārt jūs to dzerat, manai piemiņai!
26ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና።
26Un cikkārt šo maizi ēdīsiet un biķeri dzersiet, jūs pasludināsiet Kunga nāvi, iekams Viņš nāks.
27ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት።
27Tātad, kas necienīgi šo maizi ēdīs vai dzers Kunga biķeri, tas noziegsies pret Kunga Miesu un Asinīm.
28ሰው ግን ራሱን ይፈትን፥ እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤
28Bet lai cilvēks pats sevi pārbauda, un tā lai ēd no šīs maizes un dzer no šī biķera!
29ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና።
29Jo kas ēd un dzer necienīgi, tas, neizšķirdams Kunga miesu, ēd un dzer sev tiesu.
30ስለዚህ በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል።
30Tādēļ starp jums ir daudz neveselu un vāju, un daudzi aizmiguši.
31ራሳችንን ብንመረምር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤
31Ja mēs paši sevi tiesātu, tad mēs netiktu tiesāti.
32ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።
32Bet tiesādams Kungs mūs pārmāca, lai mēs reizē ar šo pasauli netiekam pazudināti.
33ስለዚህ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ ለመብላት በተሰበሰባችሁ ጊዜ እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ።
33Tātad, mani brāļi, kad jūs sapulcējaties mielastam, tad pagaidiet cits citu!
34ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ። የቀረውንም ነገር በመጣሁ ጊዜ እደነግጋለሁ።
34Ja kāds ir izsalcis, lai paēd mājās, ka jūs nesapulcētos tiesai. Kad ieradīšos, noteikšu pārējo.