1Vai es neesmu brīvs? Vai es neesmu apustulis? Vai es neesmu mūsu Kungu Jēzu Kristu redzējis? Vai jūs neesat mans darbs Kungā?
1እኔ ነጻ አይደለሁምን? ሐዋርያስ አይደለሁምን? ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንስ አላየሁትምን? እናንተስ በጌታ ሥራዬ አይደላችሁምን?
2Ja es citiem neesmu apustulis, tad jums es esmu, jo jūs esat manas apustuļa sūtības zīmogs Kungā.
2የሐዋርያነቴ ማኅተም በጌታ እናንተ ናችሁና ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን ለእናንተስ ምንም ቢሆን ሐዋርያ ነኝ።
3Mana aizstāvēšanās pret tiem, kas mani apsūdz, ir sekojoša:
3ለሚመረምሩኝ መልሴ ይህ ነው። ልንበላና ልንጠጣ መብት የለንምን?
4Vai mums nav tiesības ēst un dzert?
5እንደ ሌሎቹ ሐዋርያትና እንደ ጌታ ወንድሞች እንደ ኬፋም፥ እኅት ሚስታችንን ይዘን ልንዞር መብት የለንምን?
5Vai mums nav tiesībās ņemt līdz sievieti - māsu tāpat kā pārējiem apustuļiem un Kunga brāļiem, un Kēfam?
6ወይስ ሥራን ለመተው መብት የሌለን እኔና በርናባስ ብቻ ነን?
6Vai man vienam un Barnabam nav tiesības tā darīt?
7ከቶ በገዛ ገንዘቡ በወታደርነት የሚያገለግል ማን ነው? ወይስ ወይን ተክሎ ፍሬውን የማይበላ ማን ነው? ወይስ መንጋ እየጠበቀ ከመንጋው ወተት የማይጠጣ ማን ነው?
7Kas tad karo saviem līdzekļiem? Kas dēsta vīna dārzu un nebauda no tā augļiem? Kas gana ganāmpulku un neēd ganāmpulka pienu?
8ይህን በሰው ሥልጣን ብቻ እላለሁን?
8Vai es to runāju kā cilvēks? Vai arī likums to nesaka?
9ሕግስ ደግሞ ያን አይልምን? የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር ተብሎ በሙሴ ሕግ ተጽፎአልና። እግዚአብሔርስ ስለ በሬዎች ይገደዋልን?
9Jo Mozus likums saka: Neaizsien purnu kūlējam vērsim. (5.Moz.25,4) Vai Dievam rūp vērši?
10ይህን የሚለው ፈጽሞ ስለ እኛ አይደለምን? የሚያርስ በተስፋ ሊያርስ የሚያበራይም እንዲካፈል በተስፋ ሊያበራይ ስለሚገባው በእውነት ስለ እኛ ተጽፎአል።
10Vai to viņš nesaka mūsu dēļ? Jo mūsu dēļ ir rakstīts: arājam jāar cerībā un kulējam jākuļ cerībā saņemt ražu.
11እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆንን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን?
11Ja mēs esam jums sējuši garīgo, vai tad ir kas liels, ka mēs pļaujam jūsu laicīgo?
12ሌሎች በእናንተ ላይ ይህን መብት የሚካፈሉ ከሆኑ እኛማ ይልቁን እንዴታ? ነገር ግን የክርስቶስን ወንጌል እንዳንከለክል በሁሉ እንታገሣለን እንጂ በዚህ መብት አልተጠቀምንም።
12Ja citi ir jūsu tiesību līdzdalībnieki, kāpēc jo vairāk ne mēs? Bet mēs neesam šīs tiesības izlietojuši, un mēs visu panesam, lai Kristus evaņģēlijam neradītu šķērsļus.
13በመቅደስ ነገር የሚያገለግሉ ከመቅደስ የሆነውን ነገርን እንዲመገቡ፥ በመሠዊያውም የሚጸኑ ከመሠዊያው እንዲካፈሉ አታውቁምን?
13Vai jūs nezināt, ka tie, kas svētnīcā strādā, no svētnīcas pārtiek, un kas altārim kalpo, no altāra saņem savu daļu?
14እንዲሁ ደግሞ ወንጌልን የሚሰብኩ ከወንጌል ቀለብ እንዲቀበሉ ጌታ ደንግጎአል።
14Tāpat arī Kungs noteicis evaņģēlija sludinātājiem pārtikt no evaņģēlija.
15እኔ ግን ከእነዚህ ሁሉ ምንም አልተጠቀምሁም። እንዲህ እንዲሆንልኝ ይህን አልጽፍም፤ ማንም ትምክህቴን ከንቱ ከሚያደርግብኝ ሞት ይሻለኛልና።
15Bet es nekā no tā neesmu izlietojis. Tomēr es nerakstu, lai to uz mani attiecinātu, jo man labāk mirt, nekā kāds manu godu laupītu.
16ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።
16Jo kad es sludinu evaņģēliju, tas nav man par godu, bet tas man nepieciešami jādara. Bēdas man, ja es evaņģēliju nesludinātu!
17ይህን በፈቃዴ ባደርገው ደመወዝ አለኝና፤ ያለ ፈቃዴ ግን ባደርገው መጋቢነት በአደራ ተሰጥቶኛል።
17Jo ja es to labprāt daru, tad man ir alga, bet ja nelabprāt, tad tas man ir uzticēts amats.
18እንግዲህ ደመወዜ ምንድር ነው? ወንጌልን እየሰበክሁ በወንጌል ካለኝ መብት በሙሉ እንዳልጠቀም ወንጌልን ያለ ዋጋ ብናገር ነው።
18Kāda tad ir mana alga? Tā, ka es, evaņģēliju sludinādams, pasludinu to bez atlīdzības un neizmantoju tiesības, kādas man dod evaņģēlija sludināšana.
19ከሰው ሁሉ አርነት የወጣሁ ስሆን የሚበልጡትን እንድጠቅም እንደ ባሪያ ራሴን ለሁሉ አስገዛለሁ።
19Un es, starp visiem brīvs būdams, kļuvu visu kalps, lai iemantotu daudzus.
20አይሁድንም እጠቅም ዘንድ ከአይሁድ ጋር እንደ አይሁዳዊ ሆንሁ፤ ከሕግ በታች ያሉትን እጠቅም ዘንድ፥ እኔ ራሴ ከሕግ በታች ሳልሆን፥ ከሕግ በታች ላሉት ከሕግ በታች እንዳለሁ ሆንሁ፤
20Un jūdiem es kļuvu it kā jūds, lai iemantotu jūdus;
21ሕግ የሌላቸውን እጠቅም ዘንድ፥ ያለ እግዚአብሔር ህግ ሳልኖር ነገር ግን በክርስቶስ ሕግ በታች ሳለሁ፥ ሕግ ለሌላቸው ሕግ እንደ ሌለኝ ሆንሁ፤
21Tiem, kas padoti bauslībai, it kā arī es būtu padots bauslībai, lai iemantotu tos, kas bija padoti bauslībai (lai gan es pats nebiju padots bauslībai); tiem, kas bija bez bauslības, it kā arī es būtu bez bauslības, lai iemantotu tos, kas bija bez bauslības (kaut es nebiju bez Dieva bauslības, bet biju padots Kristus bauslībai).
22ደካሞችን እጠቅም ዘንድ ለደካሞች እንደ ደካማ ሆንሁ፤ በሁሉ መንገድ አንዳንዶችን አድን ዘንድ፥ ከሁሉ ጋር በሁሉ ነገር እንደ እነርሱ ሆንሁ።
22Vājajiem es kļuvu vājš, lai iemantotu vājos. Visiem es kļuvu viss, lai visus izglābtu.
23በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።
23Bet to visu es daru evaņģēlija dēļ, lai es būtu tā līdzdalībnieks.
24በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።
24Vai nezināt, ka tie, kas stadionā skrien, visi gan skrien, bet viens saņem godalgu? Skrieniet tā, lai jūs to saņemtu!
25የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን።
25Katrs sacīkšu dalībnieks atturas no visa, un to viņi dara, lai iegūtu iznīcīgo kroni, bet mēs - neiznīcīgo.
26ስለዚህ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም፥ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፤
26Tātad es neskrienu uz kaut ko nenoteiktu, tā es necīnos, it kā gaisu sizdams.
27ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ።
27Bet es šaustu savu miesu un lieku tai sev kalpot, lai kādreiz, citiem sludinot, pats netiktu atmests.