1Bet attiecēbā uz elkupuriem mēs zinām, ka mums visiem ir atziņa. Zināšanas dara uzpūtīgus, bet mīlestība ceļ.
1ለጣዖት ስለ ተሠዋ ሥጋም፥ ሁላችን እውቀት እንዳለን እናውቃለን። እውቀት ያስታብያል ፍቅር ግን ያንጻል።
2Bet ja kāds iedomājas, ka viņš kaut ko zina, tad tas vēl nav atzinis to, kā viņam tas jāzina.
2ማንም አንዳች የሚያውቅ ቢመስለው ሊያውቅ እንደሚገባው ገና አላወቀም፤
3Bet ja kāds mīl Dievu, to Dievs ir atzinis.
3ማንም ግን እግዚአብሔርን ቢወድ እርሱ በእርሱ ዘንድ የታወቀ ነው።
4Attiecībā uz barību, kas tiek upurēta elkiem, mēs zinām, ka elks pasaulē nav nekas un ka nav cita, bet ir tikai viens Dievs.
4እንግዲህ ለጣዖት የተሠዋውን ሥጋ ስለ መብላት፥ ጣዖት ሁሉ በዓለም ከንቱ እንደ ሆነ ከአንዱም በቀር ማንም አምላክ እንደሌለ እናውቃለን።
5Ja arī tiek runāts par dieviem debesīs vai virs zemes (kā arī par to, ka ir daudz dievu un kungu),
5መቼም ብዙ አማልክትና ብዙ ጌቶች አሉ፤ ነገር ግን በሰማይ ሆነ በምድርም ሆነ አማልክት የተባሉ ምንም ቢኖሩ፥
6Tad mums ir tikai viens Dievs, - Tēvs, no kura viss un kura dēļ mēs esam; un viens Kungs Jēzus Kristus, caur kuru viss un caur Viņu arī mēs.
6ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን፥ ነገር ሁሉም በእርሱ በኩል የሆነ እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን።
7Bet ne visos ir atziņa. Daži pieraduši vēl līdz šim pie elkiem, ēd it kā elkupuri, un tā viņu sirdsapziņa, vāja būdama, tiek apgānīta.
7ነገር ግን ይህ እውቀት በሁሉ ዘንድ አይገኝም፤ አንዳንዶች ግን ጣዖትን እስከ አሁን ድረስ ስለ ለመዱ። ለጣዖት የተሠዋ ነው ብለው ይበላሉና ሕሊናቸው ደካማ ስለ ሆነ ይረክሳል።
8Ēdiens mūs netuvina Dievam. Jo, ja ēdīsim, mēs nekļūsim labāki, un ja neēdīsim, mēs nekļūsim sliktāki.
8መብል ግን ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላም ምንም አይጎድለንም ብንበላም ምንም አይተርፈንም።
9Tomēr pielūkojiet, ka šī jūsu brīvība kādreiz nekļūst ieļaunošana vājajiem!
9ዳሩ ግን ይህ መብታችሁ ለደካሞች ዕንቅፋት እንዳይሆንባቸው ተጠንቀቁ።
10Jo ja kāds redzēs to, kam ir saprašana, elku namā piedalāmies mielastā, vai tad tā sirdsapziņa, būdama vāja, nepamudinās viņu ēst elkupurus?
10አንተ እውቀት ያለህ በጣዖት ቤት በማዕድ ስትቀመጥ አንድ ሰው ቢያይህ፥ ደካማ ሰው ቢሆን ለጣዖት የተሠዋውን ለመብላት ሕሊናው አይታነጽበትምን?
11Tā tavas saprašanas dēļ ies pazušanā vājais, par kuru Kristus ir miris.
11በአንተ እውቀትም ይህ ደካማ ይጠፋል፥ እርሱም ክርስቶስ የሞተለት ወንድም ነው።
12Bet tā, pret brāļiem grēkodami un viņu vājo sirdsapziņu ievainodami, jūs grēkojat pret Kristu.
12እንዲህም ወንድሞችን እየበደላችሁ ደካማም የሆነውን ሕሊናቸውን እያቆሰላችሁ ክርስቶስን ትበድላላችሁ።
13Tādēļ, ja ēdiens ieļauno manu brāli, es mūžam gaļu neēdīšu, lai neapgrēcinātu savu brāli.
13ስለዚህም መብል ወንድሜን የሚያሰናክለው ከሆነ፥ ወንድሜን እንዳላሰናክለው ለዘላለም ከቶ ሥጋ አልበላም።