Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

1 Corinthians

7

1Bet attiecībā uz to, ko jūs man rakstījāt: Ir labi cilvēkam sievieti neaizskart.
1ስለ ጻፋችሁልኝስ ነገር፥ ከሴት ጋር አለመገናኘት ለሰው መልካም ነው።
2Bet netiklības novēršanai lai katram ir sava sieva un katrai savs vīrs!
2ነገር ግን ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራስዋ ባል ይኑራት።
3Vīram jāizpilda pienākums pret sievu, tāpat arī sievai pret vīru.
3ባል ለሚስቱ የሚገባትን ያድርግላት፥ እንደዚሁም ደግሞ ሚስቲቱ ለባልዋ።
4Sievai nav varas pār savu miesu, bet vīram; tāpat arī vīram nav varas pār savu miesu, bet sievai.
4ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፥ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም፥ ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ።
5Neizvairieties viens no otra, kā vien uz kādu laiku, pašiem vienojoties, lai nodotos lūgšanai; bet tad atkal atgriezieties viens pie otra, lai sātans jūs nekārdinātu jūsu nesavaldības dēļ.
5ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር፥ እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ፤ ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ።
6Bet to es saku: atļaudams, ne pavēlēdams.
6ዳሩ ግን ይህን እንደ ፈቃድ እላለሁ እንጂ እንደ ትእዛዝ አይደለም።
7Jo es vēlos, ka visi būtu tā kā es; bet katram ir sava dāvana no Dieva: vienam tā, otram cita.
7ሰው ሁሉ እንደ እኔ ሊሆን እወዳለሁና፤ ነገር ግን እያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ለራሱ የጸጋ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም እንደዚያ።
8Bet es saku neprecētajiem un atraitņiem: labi viņiem būtu, ja viņi paliktu tā kā es.
8ላላገቡና ለመበለቶች ግን እላለሁ። እንደ እኔ ቢኖሩ ለእነርሱ መልካም ነው፤
9Bet ja viņi nav atturīgi, lai precas; jo labāk doties laulībā, nekā degt kaislībā.
9ነገር ግን በምኞት ከመቃጠል መጋባት ይሻላልና ራሳቸውን መግዛት ባይችሉ ያግቡ።
10Bet laulātajiem pavēlu ne es, bet Kungs: sieva lai nešķiras no vīra!
10ሚስትም ከባልዋ አትለያይ፥ ብትለያይ ግን ሳታገባ ትኑር ወይም ከባልዋ ትታረቅ፥ ባልም ሚስቱን አይተዋት ብዬ የተጋቡትን አዛቸዋለሁ፥ እኔ ግን አላዝም፥ ጌታ እንጂ።
11Un ja tā šķīrusies, tad tai jāpaliek neprecētai vai jāizlīgst ar savu vīru. Arī vīrs lai sievu neatstāj!
12ሌሎችንም እኔ እላለሁ፥ ጌታም አይደለም፤ ከወንድሞች ወገን ያላመነች ሚስት ያለችው ቢኖር እርስዋም ከእርሱ ጋር ልትቀመጥ ብትስማማ፥ አይተዋት፤
12Pārējim ne Kungs, bet es saku: ja kādam brālim ir nekristīta sieva un tā piekrīt ar viņu kopā dzīvot, tad lai viņš to neatstāj!
13ያላመነ ባል ያላት ሚስትም ብትኖር ይህ ከእርስዋ ጋር ሊቀመጥ ቢስማማ፥ አትተወው።
13Un ja kādai ticīgai sievai ir nekristīts vīrs, un tas piekrīt ar viņu kopā dzīvot, tad lai neatstāj vīru!
14ያላመነ ባል በሚስቱ ተቀድሶአልና፥ ያላመነችም ሚስት በባልዋ ተቀድሳለች፤ አለዚያ ልጆቻችሁ ርኵሳን ናቸው፤ አሁን ግን የተቀደሱ ናቸው።
14Jo ticīgā sieva svētī neticīgo vīru, un ticīgais vīrs svētī neticīgo sievu; citādi jūsu bērni būtu nešķīsti, bet tagad tie ir svēti.
15የማያምን ግን ቢለይ ይለይ፤ ወንድም ቢሆን ወይም እኅት እንዲህ በሚመስል ነገር አይገዙም፤ እግዚአብሔር ግን በሰላም ጠርቶናል።
15Bet ja nekristītais šķiras, tad lai iet, jo brālis vai māsa tādā gadījumā nav saistīti; Dievs mūs ir aicinājis mieram.
16አንቺ ሴት፥ ባልሽን ታድኚ እንደ ሆንሽ ምን ታውቂአለሽ? ወይስ አንተ ሰው፥ ሚስትህን ታድን እንደ ሆንህ ምን ታውቃለህ?
16Jo no kurienes tu, sieva, zini, ka izglābsi savu vīru? Vai no kurienes tu, vīrs, zini, ka izglābsi savu sievu?
17ብቻ ለእያንዳንዱ እግዚአብሔር እንደ ከፈለለት እያንዳንዱም እግዚአብሔር እንደ ጠራው እንዲሁ ይመላለስ። እንዲሁም በአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እደነግጋለሁ።
17Lai katrs dzīvo tā, kā katram Kungs piešķīris un kā Dievs katru aicinājis, un kā es visās draudzēs mācu.
18ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ።
18Ja kāds apgraizītais ir aicināts, tad lai viņš nemeklē neapgraizīšanas; ja kāds neapgraizītais ir aicināts, tas lai paliek neapgraizīts!
19መገረዝ ቢሆን አለመገረዝም ቢሆን ከንቱ ነው፥ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ መጠበቅ ነው እንጂ።
19Apgraizīšana nekas nav un neapgraizīšana nekas nav, bet Dieva baušļu pildīšana.
20እያንዳንዱ በተጠራበት መጠራት እንደዚሁ ይኑር።
20Katrs lai paliek tanī aicinājumā, kurā tas aicināts!
21ባሪያ ሆነህ ተጠርተህ እንደ ሆነ አይገድህም፤ አርነት ልትወጣ ቢቻልህ ግን አርነትን ተቀበል።
21Ja esi aicināts vergs, nezūdies par to, bet, ja vari kļūt brīvs, tad izmanto to!
22ባሪያ ሆኖ በጌታ የተጠራ የጌታ ነጻ ነውና፤ እንዲሁም ነጻ ሆኖ የተጠራ የክርስቶስ ባሪያ ነው።
22Jo kas, vergs būdams, ir Kunga aicināts, tas ir Kunga brīvlaistais; līdzīgi tas, kas brīvs būdams, aicināts, ir Kristus kalps.
23በዋጋ ተገዝታችኋል፤ የሰው ባሪያዎች አትሁኑ።
23Jūs esat dārgi atpirkti, nekļūstiet cilvēku vergi!
24ወንድሞች ሆይ፥ እያንዳንዱ በተጠራበት እንደዚሁ ሆኖ በእግዚአብሔር ዘንድ ይኑር።
24Brāļi, katrs lai paliek Dieva priekšā, kā viņš ir aicināts!
25ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም፥ ነገር ግን የታመንሁ እሆን ዘንድ ከጌታ ምሕረትን የተቀበልሁ እንደ መሆኔ ምክር እመክራለሁ።
25Attiecībā uz jaunavību man Kunga pavēles nav, bet es dodu padomu kā tāds, kas no Kunga ieguvis žēlsirdību, lai būtu uzticīgs.
26እንግዲህ ስለ አሁኑ ችግር ይህ መልካም ይመስለኛል፤ ሰው እንዲህ ሆኖ ቢኖር መልካም ነው።
26Tāpēc pašreizējo spaidu dēļ es atzīstu par labāku, ka cilvēkam labāk palikt tāpat.
27በሚስት ታስረህ እንደ ሆንህ መፋታትን አትሻ፤ በሚስት አልታሰርህ እንደ ሆንህ ሚስትን አትሻ።
27Ja esi saistīts ar sievu, nemeklē šķiršanos; ja esi neprecēts, nemeklē sievu!
28ብታገባ ግን ኃጢአት አትሠራም ድንግሊቱም ብታገባ ኃጢአት አትሠራም፤ ነገር ግን እንዲህ በሚያደርጉ በሥጋቸው ላይ መከራ ይሆንባቸዋል፥ እኔም እራራላችሁ ነበር።
28Bet ja esi devies laulībā, tad neesi grēkojis; un ja jaunava apprecas, tā negrēko, bet miesas grūtības viņiem būs. Es tomēr gribu jūs saudzēt.
29ዳሩ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እናገራለሁ፤ ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው ይሁኑ፥
29Brāļi, tāpēc es to saku: laiks ir īss. Turpmāk, lai tie, kam ir sievas, būtu tādi, it kā viņiem tās nebūtu;
30የሚያለቅሱም እንደማያለቅሱ፥ ደስ የሚላቸውም ደስ እንደማይላቸው፥
30Un tie, kas raud, kā tādi, kas neraud; un kas priecājas, kā tādi, kas nepriecājas; un kas pērk, kā tādi, kam nekā nav;
31የሚገዙም ምንም እንደሌላቸው፥ በዚችም ዓለም የሚጠቀሙ በሙሉ እንደማይጠቀሙባት ይሁኑ፤ የዚች ዓለም መልክ አላፊ ነውና።
31Un kas šo pasauli izmanto, būtu kā tādi, kas to neizmanto, jo šīs pasaules veids iznīkst.
32ነገር ግን ያለ አሳብ ልትኖሩ እወዳለሁ። ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ እንዲያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል፤
32Bet es vēlos, lai jūs būtu bez rūpēm. Kam nav sievas, tas rūpējas par to, kas ir Kunga, kā patikt Dievam.
33ያገባው ግን ሚስቱን እንዴት ደስ እንዲያሰኛት የዓለምን ነገር ያስባል፥ ልቡም ተከፍሎአል።
33Bet precētais rūpējas par pasaules lietām, kā patikt sievai, un viņš ir dalīts.
34ያልተጋባች ሴትና ድንግል በሥጋም በነፍስም እንዲቀደሱ የጌታን ነገር ያስባሉ፤ የተጋባች ግን ባልዋን እንዴት ደስ እንድታሰኘው የዓለምን ነገር ታስባለች።
34Arī neprecētā sieviete un jaunava domā par to, kas ir Kunga, lai būtu svēta miesā un garā; bet precētā domā par pasaules lietām, kā patikt vīram.
35ይህንም ለራሳችሁ ጥቅም እላለሁ፤ በአገባብ እንድትኖሩ ሳትባክኑም በጌታ እንድትጸኑ ነው እንጂ ላጠምዳችሁ ብዬ አይደለም።
35Es to saku jūsu labā, ne cilpu jums apmezdams, bet tājā nolūkā, lai dotu jums iespēju godīgā dzīvē un bez traucējuma pielūgt Kungu.
36ዳሩ ግን ማግባት ወደሚገባው ዕድሜ በደረሰ ጊዜ ስለ ድንግልናው ያፈረ ሰው ቢኖር፥ የወደደውን ያድርግ፤ ኃጢአት የለበትም፤ ይጋቡ።
36Bet ja kādam šķiet, ka izrādīsies necienīgi, ja viņa jaunava būs pāri gadiem, un tam tā jānotiek, tad lai dara, kā grib! Ja viņa dodas laulībā, grēka nav.
37ሳይናወጥ በልቡ የጸና ግን ግድ የለበትም፥ የወደደውን እንዲያደርግ ተፈቅዶለታል፤ ድንግልናውንም በልቡ ይጠብቅ ዘንድ ቢጸና፥ መልካም አደረገ።
37Bet kas, nebūdams padots nekādai nepieciešamībai, noteikti nospriedis savā sirdī un, rīkojoties saskaņā ar savu brīvo gribu, ir nolēmis savā sirdī paturēt savu meitu jaunavībā, tas labi dara.
38እንዲሁም ድንግልን ያገባ መልካም አደረገ ያላገባም የተሻለ አደረገ።
38Tātad, kas savu meitu atdod pie vīra, tas labi dara, bet kas nedod pie vīra, tas dara labāk.
39ሴት ባልዋ በሕይወት ሳለ የታሰረች ናት፤ ባልዋ ቢሞት ግን በጌታ ይሁን እንጂ የወደደችውን ልታገባ ነጻነት አላት።
39Sieva ir padota likumam, kamēr viņas vīrs dzīvs. Ja tās vīrs ir miris, viņa ir brīva un var doties laulībā, ar ko vēlas, bet tikai Kungā.
40እንደ ምክሬ ግን እንዳለች ብትኖር ደስተኛ ናት፤ እኔም ደግሞ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ያለ ይመስለኛል።
40Bet svētīgāka viņa būs, ja saskaņā ar manu padomu paliks tāpat. Es esmu pārliecināts, ka arī man ir Dieva Gars.