Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

1 Peter

3

1Tāpat arī, sievas, paklausiet saviem vīriem, lai arī tie, kas netic vārdam, pateicoties sievas dzīvei, tiktu iegūti bez sludināšanas,
1እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው።
2Kad redzēs jūsu dievbijīgi skaidro dzīvi. (Ef 5,22; Kol 3,18)
3ለእናንተም ጠጕርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ፥
3Jūsu greznums lai nav ārējais matu pinums, zelta rotas vai grezni apģērbi,
4ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።
4Bet apslēptais sirds cilvēks, neiznīcīgs savā klusajā un maigajā garā, kas Dievam dārgs!
5እንዲህ በቀድሞ ዘመን በእግዚአብሔር ተስፋ ያደረጉት ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ ለባሎቻቸው ሲገዙ ተሸልመው ነበርና፤
5Jo tā kādreiz greznojās svētās sievietes, kas cerēja uz Dievu, būdamas paklausīgas saviem vīriem,
6እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም። ጌታ ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፤ እናንተም ከሚያስደነግጥ ነገር አንዳች እንኳ ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ ልጆችዋ ናችሁ።
6Kā Sāra bija paklausīga Ābrahamam, saukdama to par kungu. Jūs esat viņas meitas, kad darāt labu un nebīstieties nekādu draudu.
7እንዲሁም፥ እናንተ ባሎች ሆይ፥ ደካማ ፍጥረት ስለ ሆኑ ከሚስቶቻችሁ ጋር በማስተዋል አብራችሁ ኑሩ፤ ጸሎታችሁ እንዳይከለከል አብረው ደግሞ የሕይወትን ጸጋ እንደሚወርሱ አድርጋችሁ አክብሩአቸው።
7Tāpat jūs vīri, sadzīvojiet prātīgi ar sievām kā ar trauslāku trauku! Parādiet viņām godu kā žēlastības dzīves līdzmantiniecēm, lai jūsu lūgšanas netiktu traucētas!
8በመጨረሻው ሁላችሁ በአንድ ልብ ሁኑ፥ የሌላው መከራ ለእናንተ እንደሚሆን አድርጉ፥ እንደወንድሞች ተዋደዱ፥ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ፤
8Bet beidzot esiet visi vienprātīgi, līdzcietīgi, brālīgi, žēlsirdīgi, pacietīgi, pazemīgi!
9ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ ለዚህ ተጠርታችኋልና።
9Neatmaksājiet ļaunu ar ļaunu, nedz lāstus ar lāstiem, turpretim svētiet, jo tam jūs esat aicināti, lai iemantotu svētību.
10ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል፤
10Jo, kas mīl dzīvi un grib redzēt labas dienas, tas lai savalda savu mēli no ļauna, un tā lūpas lai nerunā viltu!
11ከክፉ ፈቀቅ ይበል፥ መልካምንም ያድርግ፥ ሰላምን ይሻ ይከተለውም፤
11Izvairies no ļauna un dari labu, meklē mieru un centies, un seko tam!
12የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ ጆሮዎቹም ለጸሎታቸው ተከፍተዋል፥ የጌታ ፊት ግን ክፉ ነገርን በሚያደርጉ ላይ ነው።
12Jo Kunga acis ievēro taisnīgos, un Viņa ausis dzird to lūgšanas, bet Kunga vaigs ir pret tiem, kas dara ļaunu.
13በጎንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው?
13Un kas jums varēs kaitēt, ja jūs dedzīgi centīsieties pēc laba?
14ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብፁዓን ናችሁ። ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ አትናወጡም፥
14Bet ja arī jūs ciestu taisnības dēļ, tad jūs esat svētīgi. Bet nebīstieties no viņiem un neuztraucieties!
15ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስ በልባችሁ ቀድሱት። በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።
15Bet svētiet Kungu Jēzu Kristu savās sirdīs! Esiet vienmēr gatavi atlīdzināt katram, kas prasa no jums norēķinu par to cerību, kas ir jūsos!
16በክርስቶስ ያለውን መልካሙን ኑሮአችሁን የሚሳደቡ ሰዎች ክፉን እንደምታደርጉ በሚያሙበት ነገር እንዲያፍሩ በጎ ሕሊና ይኑራችሁ።
16Tomēr lēnprātībā un bijībā, lai jums būtu laba sirdsapziņa, lai kaunas tie, kas jums ceļ neslavu, nopeļot jūsu labo dzīvi Kristū.
17የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲህ ቢሆን፥ ክፉ ስለ ማድረግ ሳይሆን በጎ ስለ ማድረግ መከራን ብትቀበሉ ይሻላችኋልና።
17Jo labāk, labu darot, ciest, jo tāds ir Dieva prāts, nekā darīt ļaunu.
18ክርስቶስ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር እንዲያቀርበን እርሱ ጻድቅ ሆኖ ስለ ዓመፀኞች አንድ ጊዜ በኃጢአት ምክንያት ሞቶአልና፤ በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ፥
18Jo arī Kristus vienreiz mūsu grēku dēļ miris. Taisnīgais par netaisnīgajiem, nonāvēts gan miesā, bet atdzīvināts garā, lai mūs upurētu Dievam.
19በእርሱም ደግሞ ሄዶ በወኅኒ ለነበሩ ነፍሳት ሰበከላቸው፤
19Garā Viņš nogāja un sludināja tiem gariem, kas bija cietumā.
20ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ፥ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቈየ ጊዜ ቀድሞ አልታዘዙም።
20Kuri kādreiz neticēja, kad tie Noasa dienās paļāvās uz Dieva pacietību, kamēr taisīja šķirstu, kurā no ūdens izglābās nedaudzi, proti, astoņas dvēseles;
21ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቅት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፥ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፥ ለእግዚአብሔር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፥ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው፤
21Tas attēlo kristību, kura tagad arī jūs izglābj. Tā nav miesas netīrību nomazgāšana, bet Dievam veltīta lūgšana labā sirdsapziņā caur Jēzus Kristus augšāmcelšanos.
22እርሱም መላእክትና ሥልጣናት ኃይላትም ከተገዙለት በኋላ ወደ ሰማይ ሄዶ በእግዚአብሔር ቀኝ አለ።
22Lai mēs kļūtu mūžīgās dzīves mantinieki, Viņš, nāvi uzvarējis, uzgāja debesīs un sēž pie Dieva labās rokas, kur Viņam pakļauti eņģeļi, varas un spēki.