Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

2 Corinthians

2

1Bet es pats sevī apņēmos pie jums ar skumjām vairs nenākt.
1ነገር ግን ዳግመኛ በኀዘን ወደ እናንተ እንዳልመጣ ስለ እኔ ቆረጥሁ።
2Jo ja es jūs apbēdinu, tad kas mani iepriecinās, ja ne tas, ko es apbēdināju?
2እኔስ ባሳዝናችሁ፥ እንግዲያስ በእኔ ምክንያት ከሚያዝን በቀር ደስ የሚያሰኘኝ ማን ነው?
3Tāpēc es jums to rakstīju, lai, atnākot, man nebūtu bēdas uz bēdām par tiem, par kuriem man vajadzēja priecāties; es uzticos jums visiem, jo mans ir arī jūsu visu prieks.
3ደስ ሊያሰኙኝ ከሚገባቸውም በመምጣቴ ኀዘን እንዳይሆንብኝ ይህንኑ ጻፍሁላችሁ፥ ደስታዬ የሁላችሁ ደስታ ነው ብዬ በሁላችሁ ታምኜአለሁና።
4Jo es jums rakstīju lielās bēdās un sirds bailēs, rūgti raudādams, nevis lai jūs skumtu, bet lai jūs zinātu, cik ļoti es jūs mīlu.
4በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችሁ ነበርና፤ ይህም እናንተን አብዝቼ የምወድበትን ፍቅር እንድታውቁ እንጂ እንዳሳዝናችሁ አይደለም።
5Ja kāds apbēdināja, tad ne mani vien, bet, lai neapvainotu visus, pa daļai arī jūs.
5ነገር ግን ማንም አሳዝኖ ቢሆን፥ እንዳልከብድባችሁ፥ በክፍል ሁላችሁን እንጂ እኔን ያሳዘነ አይደለም።
6Tādam pietiek soda, ko vairākums viņam uzlicis.
6እንደዚህ ላለ ሰው ይህ ከእናንተ የምትበዙት የቀጣችሁት ቅጣት ይበቃዋልና እንደዚህ ያለው ከልክ በሚበዛ ኀዘን እንዳይዋጥ፥
7Pretēji tam labāk piedodiet un ieprieciniet viņu, lai to nenomāc pārāk lielas bēdas!
7ይልቅ ተመልሳችሁ ይቅር ማለትና ማጽናናት ይገባችኋል።
8Tāpēc es jūs uzaicinu, lai jūs parādītu viņam mīlestību.
8ስለዚህ ከእርሱ ጋር ፍቅርን እንድታጸኑ እለምናችኋለሁ፤
9Jo tamdēļ es jums arī rakstīju, lai pārliecinātos par jums, vai jūs visā esat paklausīgi.
9ስለዚህ ደግሞ ጽፌ ነበርና፤ በሁሉ የምትታዘዙ እንደ ሆናችሁ የእናንተን መፈተን አውቅ ዘንድ አሳቤ ነበር።
10Bet kam jūs ko piedevāt, tam arī es piedevu; jo ja es kādam piedevu, tad piedevu jūsu dēļ Kristus vārdā,
10እናንተ ግን ይቅር የምትሉትን እኔ ደግሞ ይቅር እለዋለሁ፤ እኔም ይቅር ካልሁ፥ ይቅር ያልሁትን ስለ እናንተ በክርስቶስ ፊት ይቅር ብዬአለሁ፥
11Lai sātans mūs nepieviltu, jo viņa nodomi mums ir zināmi.
11በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና።
12Bet kad es nonācu Troadā Kristus evaņģēlija dēļ un durvis Kungā man bija atvērtas,
12ስለ ክርስቶስም ወንጌል ወደ ጢሮአዳ በመጣሁ ጊዜ፥ ለጌታ ሥራ በር ምንም ቢከፈትልኝ፥ ቲቶን ወንድሜን ስላላገኘሁት መንፈሴ ዕረፍት አልነበረውም፥
13Mans gars neatrada mieru, tāpēc ka nesastapu savu brāli Titu. Atvadījies no viņiem, es aizgāju uz Maķedoniju.
13ነገር ግን ከእነርሱ ተሰናብቼ ወደ መቄዶንያ ወጣሁ።
14Bet lai pateicība Dievam, kas mums liek uzvarēt Jēzū Kristū un caur mums izplata Viņa atziņas smaržu visās vietās,
14ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤
15Jo Dievam mēs esam Kristus labā smarža tiem, kas tiek izglābti, un tiem, kas iet pazušanā:
15በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤
16Vieniem gan nāves smarža nāvei, bet citiem dzīvības smarža dzīvībai. Un kas tam ir piemērots?
16ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?
17Mēs neviltojam Dieva vārdu kā daudzi citi, bet mēs runājam no skaidras sirds kā no Dieva, - Dieva priekšā, Kristus vārdā.
17የእግዚአብሔርን ቃል ቀላቅለው እንደሚሸቃቅጡት እንደ ብዙዎቹ አይደለንምና፤ በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ ተላክን በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።