1Tāpēc, ja jūs kopā ar Kristu esat augšāmcēlušies, tad meklējiet pēc tā, kas augšā, kur Kristus sēž pie Dieva labās rokas!
1እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ።
2Domājiet par to, kas augšā, bet ne par to, kas virs zemes!
2በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም።
3Jo jūs mirāt, bet jūsu dzīvība līdz ar Kristu apslēpta Dievā.
3ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና።
4Kad parādīsies Kristus, jūsu dzīvība, tad arī jūs parādīsieties godībā līdz ar Viņu.
4ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ፥ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ።
5Tāpēc nonāvējiet savos locekļos zemisko: netiklību, nešķīstību, kaislību, ļaunās kārības un mantkārību, kas ir kalpošana elkiem!
5እንግዲህ በምድር ያሉቱን ብልቶቻችሁን ግደሉ፥ እነዚህም ዝሙትና ርኵሰት ፍትወትም ክፉ ምኞትም ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው።
6Tā visa dēļ nāk Dieva dusmas pār netiklības bērniem.
6በእነዚህም ጠንቅ የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ይመጣል።
7Arī jūs kādreiz bijāt tām pakļāvušies, kad tanīs dzīvojāt.
7እናንተም ደግሞ ትኖሩባቸው በነበራችሁ ጊዜ፥ በፊት በእነዚህ ተመላለሳችሁ።
8Bet tagad arī jūs atmetiet to visu: dusmas, sarūgtinājumu, ļaunprātību, zaimus un nekaunīgus vārdus no jūsu mutes!
8አሁን ግን እናንተ ደግሞ ቍጣንና ንዴትን ክፋትንም፥ ከአፋችሁም ስድብን የሚያሳፍርንም ንግግር እነዚህን ሁሉ አስወግዱ።
9Nemelojiet viens otram! Novelciet veco cilvēku kopā ar viņa darbiem
9እርስ በርሳችሁ ውሸት አትነጋገሩ፥ አሮጌውን ሰው ከሥራው ጋር ገፋችሁታልና፥
10Un apģērbiet jauno, kas atjaunojas atziņā saskaņā ar viņa Radītāja attēlu,
10የፈጠረውንም ምሳሌ እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው ለብሳችሁታል።
11Kur vairs nav ne pagāna, ne jūda, ne apgraizītā, ne neapgraizīta, ne barbara, ne skita, ne verga, ne brīvā, bet viss un visos ir Kristus.
11በዚያም የግሪክ ሰው አይሁዳዊም የተገረዘም ያልተገረዘም አረማዊም እስኩቴስም ባሪያም ጨዋ ሰውም መሆን አልተቻለም፥ ነገር ግን ክርስቶስ ሁሉ ነው፥ በሁሉም ነው።
12Tāpēc kā Dieva izredzētie, svētie un mīlētie tērpieties sirsnīgā žēlsirdībā, laipnībā, pazemībā, lēnprātībā, pacietībā,
12እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ።
13Viens otru paciezdami un cits citam piedodami, ja vienam pret otru ir kāda sūdzība: kā Kungs jums piedevis, tā arī jūs.
13እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ ይቅር ተባባሉ። ክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ።
14Bet pāri visam tam lai jums ir mīlestība, kas ir pilnības saite!
14በእነዚህም ሁሉ ላይ የፍጻሜ ማሰሪያ የሆነውን ፍቅርን ልበሱት።
15Un Kristus miers lai gavilē jūsu sirdīs, kam jūs esat aicināti vienā miesā! Esiet pateicīgi!
15በአንድ አካልም የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ። የምታመሰግኑም ሁኑ።
16Kristus vārds lai bagātīgi mājo jūsos, pamāciet un pamudiniet viens otru visā gudrībā! Pateicībā Dievam dziediet savās sirdīs psalmus, slavas dziesmas un garīgās dziesmas!
16የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ። በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ።
17Un visu, ko jūs darāt vārdos vai darbos, to visu dariet Kunga Jēzus Kristus vārdā, pateikdamies Dievam un Tēvam caur Viņu!
17እግዚአብሔር አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት።
18Sievas, esiet padotas saviem vīriem, jo tā tam jābūt Kunga vārdā.
18ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ።
19Vīri, mīliet savas sievas un neesiet skarbi pret viņām!
19ባሎች ሆይ፥ ሚስቶቻችሁን ውደዱ መራራም አትሁኑባቸው።
20Bērni, paklausiet visur saviem vecākiem, jo tā tas patīk Kungam.
20ልጆች ሆይ፥ ይህ ለጌታ ደስ የሚያሰኝ ነውና በሁሉ ለወላጆቻችሁ ታዘዙ።
21Tēvi, nekaitiniet savus bērnus, lai tie nekļūtu mazdūšīgi!
21አባቶች ሆይ፥ ልባቸው እንዳይዝል ልጆቻችሁን አታበሳጩአቸው።
22Kalpi, paklausiet visā saviem šīs zemes kungiem, kalpodami nevien acu priekšā, it kā gribēdami cilvēkiem izpatikt, bet sirds vienkāršībā un Dieva bijībā!
22ባሪያዎች ሆይ፥ በቅን ልብ ጌታን እየፈራችሁ እንጂ፥ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ ሳትሆኑ፥ በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ በሁሉ ታዘዙ።
23Visu, ko jūs darāt, dariet no sirds it kā Dievam, bet ne cilvēkiem,
23ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፥ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉት፥
24Zinādami, ka jūs mantojuma algu saņemsiet no Kunga. Kalpojiet Kungam Kristum!
24ከጌታ የርስትን ብድራት እንድትቀበሉ ታውቃላችሁና። የምታገለግሉት ጌታ ክርስቶስ ነውና።
25Jo kas netaisnību dara, tas saņems to, ko viņš netaisnīgi padarījis; Dievs nevērtē personu pēc tās stāvokļa.
25የሚበድልም የበደለውን በብድራት ይቀበላል፥ ለሰው ፊትም አድልዎ የለም።