Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Ephesians

1

1Pāvils, saskaņā ar Dieva prātu Jēzus Kristus apustulis, visiem svētajiem, kas atrodas Efezā, un ticīgajiem Jēzū Kristu.
1በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ፥ በኤፌሶን ላሉት ቅዱሳን በክርስቶስ ኢየሱስም ላሉት ምእመናን፤
2Žēlastība jums un miers no Dieva, mūsu Tēva, un Kunga Jēzus Kristus!
2ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
3Lai slavēts Dievs, mūsu Kunga Jēzus Kristus Tēvs, kas mūs Kristū svētījis visādā garīgā svētībā debesīs.
3በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።
4Viņā Viņš mūs izredzējis pirms pasaules radīšanas, lai mēs mīlestībā būtu svēti un nevainīgi Viņa priekšā.
4ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።
5Iepriekš paredzējis, Viņš savā labprātībā nolēma mūs pieņemt sev par bērniem caur Jēzu Kristu,
5በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን።
6Par slavu savas žēlastības godībai, ar kuru Viņš mūs apveltījis savā mīļotajā Dēlā.
6በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ።
7Viņā mums pestīšana caur Viņa asinīm, grēku piedošana saskaņā ar Viņa žēlastības bagātību,
7በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።
8Kas pārpilnībā piešķirta mums visā gudrībā un saprašanā,
8ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን።
9Lai zināmu darītu mums savas gribas noslēpumu pēc labpatikas; un tā viņš sevī bija nolēmis,
9በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤
10Laikiem piepildoties, visu, kas debesīs un kas virs zemes, atjaunot Kristū.
10በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።
11Viņā, kas dara visu pēc savas gribas lēmuma, arī mēs esam aicināti mantinieki saskaņā ar Viņa nodomu,
11እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ፥ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን።
12Lai mēs, kas jau iepriekš cerējām uz Kristu, būtu Viņa godības slava.
12ይኸውም፥ በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን እኛ ለክብሩ ምስጋና እንሆን ዘንድ ነው።
13Viņā, kad dzirdējāt patiesības vārdu (savas pestīšanas evaņģēliju) un ticējāt uz Viņu, jūs tikāt apzīmogoti ar apsolīšanas Svēto Garu.
13እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤
14Viņš ir mūsu mantojuma ķīla, lai atpestītu savu īpašumu savas godības slavai.
14እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ፥ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል።
15Tāpēc arī, dzirdēdams par jūsu ticību uz Kungu Jēzu un mīlestību uz visiem svētajiem,
15ስለዚህ እኔ ደግሞ በእናንተ ዘንድ ስለሚሆን በጌታ በኢየሱስ ስለ ማመንና ለቅዱሳን ሁሉ ስለሚሆን መውደድ ሰምቼ፥
16Es nemitējos pateikties par jums, pieminēdams jūs savās lūgšanās.
16ስለ እናንተ እያመሰገንሁ ስጸልይ ስለ እናንተ ማሳሰብን አልተውም፤
17Lai Dievs, mūsu Kunga Jēzus Kristus godības Tēvs, dod jums gudrības un atklāsmes garu Viņa pazīšanai,
17የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።
18Apgaismotu jūsu sirds acis, lai jūs zinātu, kāda ir Viņa aicinājuma cerība un cik bagāta Viņa mantojuma godība starp svētajiem.
18ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
19Un cik pārmērīgi liels ir Viņa spēks mūsos, kas ticam saskaņā ar Viņa spēka varenības izpausmi.
20ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም ከኃይልም ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው በክርስቶስ ባደረገው ሥራ የብርታቱ ጉልበት ይታያል፤
20To Viņš parādīja Kristū, uzmodinādams Viņu no miroņiem un novietodams pie savas labās rokas debesīs
22ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው።
21Augstāk par katru valdību un varu, un spēku, un valdniekiem, un par ikvienu vārdu, kas tiek piesaukts ne tikai šinī, bet arī nākamajā pasaulē.
23እርስዋም አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት።
22Un visu Viņš nolicis zem Viņa kājām un iecēla Viņu par galvu visai Baznīcai.
23Kas ir Viņa miesa un Viņa pilnība, kas visu visumā piepilda.