Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Galatians

6

1Brāļi, ja kāds cilvēks ir kritis grēkā, tad jūs, kas esat garīgi, lēnprātības garā pamāciet viņu, un lūko pats sevi, ka arī tu netieci kārdināts!
1ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት፤ አንተ ደግሞ እንዳትፈተን ራስህን ጠብቅ።
2Cits cita nastas nesiet, un tā jūs izpildīsiet Kristus likumu.
2ከእናንተ እያንዳንዱ የአንዱን ሸክም ይሸከም እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ።
3Un ja kāds, nebūdams nekas, domā, ka viņš kas ir, tas pieviļ sevi.
3አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና።
4Ikviens lai pārbauda savu darbu, tad viņam būs gods tikai sevī, bet ne pie cita.
4ነገር ግን እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሥራ ይፈትን፥ ከዚያም በኋላ ስለ ሌላው ሰው ያልሆነ ስለ ራሱ ብቻ የሚመካበትን ያገኛል፤
5Jo katram jānes sava nasta.
5እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሸክም ሊሸከም ነውና።
6Bet tas, kas tiek pamācīts vārdos, lai dalās visos labumos ar to, kas viņu pamāca.
6ነገር ግን ቃሉን የሚማር ከሚያስተምረው ጋር መልካምን ነገር ሁሉ ይከፋፈል።
7Nepievilieties, Dievs neļauj sevi izsmiet.
7አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤
8Jo ko cilvēks sēs, to arī pļaus. Kas sēj savā miesā, tas no miesas pļaus iznīcību, bet kas sēj garā, tas no gara pļaus mūžīgo dzīvi.
8በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል።
9Nepagursim, labu darīdami, jo savā laikā mēs nepagurdami arī pļausim.
9ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።
10Tātad, darīsim labu visiem, kamēr mums ir laiks, bet sevišķi ticības brāļiem.
10እንግዲያስ ጊዜ ካገኘን ዘንድ ለሰው ሁሉ ይልቁንም ለሃይማኖት ቤተ ሰዎች መልካም እናድርግ።
11Redziet, kādiem burtiem es jums pašrocīgi rakstu!
11እንዴት ባሉ ታላላቆች ፊደላት በእጄ እንደ ጻፍሁላችሁ እዩ።
12Tie, kas grib patikt miesai, uzspiež jums apgraizīšanu, lai tikai netiktu vajāti Kristus krusta dēļ.
12በሥጋ መልካም ሆነው ሊታዩ የሚወዱ ሁሉ እንድትገረዙ ግድ አሉአችሁ፥ ነገር ግን ስለ ክርስቶስ መስቀል እንዳይሰደዱ ብቻ ነው።
13Bet arī apgraizītie nepilda likumu; viņi grib, ka jūs ļautu apgraizīties, lai lielītos ar jūsu miesām.
13በሥጋችሁ እንዲመኩ ልትገረዙ ይወዳሉ እንጂ የተገረዙቱ ራሳቸው እንኳ ሕግን አይጠብቁም።
14Bet es negribu ne ar ko lepoties, tik vien ar mūsu Kunga Jēzus Kristus krustu, ar ko man pasaule krustā sista un es pasaulei.
14ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።
15Jo Kristū Jēzū nav nozīmes ne apgraizīšanai, ne neapgraizīšanai, bet gan jaunai radībai.
15በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።
16Un visiem tiem, kas sekos šiem pamatlikumiem, arī Dieva izraēliešiem, lai miers un žēlastība!
16በዚህም ሥርዓት በሚመላለሱ ሁሉ ላይ በእግዚአብሔር እስራኤልም ላይ ሰላምና ምሕረት ይሁን።
17Turpmāk lai mani neviens vairs neapgrūtina, jo es nesu savā miesā Kunga Jēzus rētas.
17እኔ የኢየሱስን ማኅተም በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ስንኳ አያድክመኝ።
18Brāļi, mūsu Kunga Jēzus Kristus žēlastība lai ir ar jūsu garu! Amen.
18ወንድሞች ሆይ፥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን። አሜን።