Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Hebrews

13

1Brāļu mīlestība lai paliek jūsos!
1የወንድማማች መዋደድ ይኑር። እንግዶችን መቀበል አትርሱ፤ በዚህ አንዳንዶች ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።
2Neaizmirstiet viesmīlību, jo daži caur to, pašiem nezinot, uzņēmuši savā pajumtē eņģeļus.
3ከእነርሱ ጋር እንደ ታሰረ ሆናችሁ እስሮችን አስቡ፥ የተጨነቁትንም ራሳችሁ ደግሞ በሥጋ እንዳለ ሆናችሁ አስቡ።
3Atminieties cietumniekus, it kā jūs kopā ar viņiem būtu cietumnieki, un cietējus, jo arī jūs vēl miesā dzīvojat.
4መጋባት በሁሉ ዘንድ ክቡር መኝታውም ንጹሕ ይሁን፤ ሴሰኞችንና አመንዝሮችን ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል።
4Laulība lai ir visā godā un laulības gulta neaptraipīta, jo netiklos un laulības pārkāpējus tiesās Dievs.
5አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤ እርሱ ራሱ። አልለቅህም ከቶም አልተውህም ብሎአልና፤
5Jūsu dzīvei jābūt brīvai no mantkārības. Apmierinieties ar to, kas jums ir, jo Viņš sacījis: Es tevi nedz atstāšu, nedz pametīšu; (5 Moz 31,6; Joz 1,5)
6ስለዚህ በድፍረት። ጌታ ይረዳኛልና አልፈራም፤ ሰው ምን ያደርገኛል? እንላለን።
6Tā ka varam droši sacīt: Kungs ir mans palīgs, es nebīstos; ko spēj man padarīt cilvēks? (Ps 117,6)
7የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።
7Atminieties savus priekšniekus, kas jums sludinājuši Dieva vārdu! Vērodami viņu dzīves iznākumu, sekojiet to ticībai!
8ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።
8Jēzus Kristus vakar un šodien, un mūžīgi tas pats.
9ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ፤ ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም፤ በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና።
9Neļaujiet sevi maldināt dažādām svešām mācībām, jo labāk, ka sirdi stiprina žēlastība, ne ēdieni; tie neko nepalīdzēja tiem, kas tanī piedalījās.
10መሠዊያ አለን፥ ከእርሱም ሊበሉ ድንኳኒቱን የሚያገለግሉ መብት የላቸውም።
10Mums ir altāris; no tā ēst nav tiesības tiem, kas kalpo teltij.
11ሊቀ ካህናት ስለ ኃጢአት ወደ ቅድስት የእንስሶችን ደም ያቀርባልና፤ ሥጋቸው ግን ከሰፈሩ ውጭ ይቃጠላል።
11Jo kuru dzīvnieku asinis augstais priesteris ienes vissvētākajā vietā, to miesas tiek sadedzinātas ārpus nometnes.
12ስለዚህ ኢየሱስ ደግሞ በገዛ ደሙ ሕዝቡን እንዲቀድስ ከበር ውጭ መከራን ተቀበለ።
12Tāpēc arī Jēzus, lai ar savām asinīm svētdarītu tautu, cieta ārpus vārtiem.
13እንግዲህ ነቀፌታውን እየተሸከምን ወደ እርሱ ወደ ሰፈሩ ውጭ እንውጣ፤
13Iziesim tad arī mēs pie Viņa ārpus nometnes, nesdami Viņa pazemošanu!
14በዚህ የምትኖር ከተማ የለችንምና፥ ነገር ግን ትመጣ ዘንድ ያላትን እንፈልጋለን።
14Jo mums šeit nav paliekamas vietas, bet mēs meklējam nākamo. (Mih.2,10)
15እንግዲህ ዘወትር ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት፥ ማለት ለስሙ የሚመሰክሩ የከንፈሮችን ፍሬ፥ በእርሱ እናቅርብለት።
15Upurēsim tad caur Viņu Dievam vienmēr slavas upuri, tas ir, mūsu lūpu augļus, kas godina Viņa vārdu.
16ነገር ግን መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና።
16Neaizmirstiet darīt labu un dot dāvanas! Tādi upuri Dievam labpatīk.
17ለዋኖቻችሁ ታዘዙና ተገዙ፤ እነርሱ ስሌትን እንደሚሰጡ አድርገው፥ ይህንኑ በደስታ እንጂ በኃዘን እንዳያደርጉት፥ ይህ የማይጠቅማችሁ ነበርና፥ ስለ ነፍሳችሁ ይተጋሉ።
17Paklausiet saviem priekšniekiem un esiet viņiem padevīgi, jo viņi ir nomodā un viņiem būs jādod norēķins par jūsu dvēselēm; lai viņi to dara priecādamies, ne nopūzdamies, jo tas jums labumu nenes.
18ጸልዩልን፤ በነገር ሁሉ በመልካም እንድንኖር ወደን፥ መልካም ሕሊና እንዳለን ተረድተናልና።
18Lūdziet Dievu par mums! Mēs apzināmies, ka mūsu sirdsapziņa ir tīra, jo visu gribam labi darīt.
19ይልቁንም ፈጥኜ እንድመለስላችሁ ይህን ታደርጉ ዘንድ አጥብቄ እለምናችኋለሁ።
19Un jo vairāk es jūs lūdzu tā darīt, lai drīzāk mani atdotu jums.
20በዘላለም ኪዳን ደም ለበጎች ትልቅ እረኛ የሆነውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ያወጣው የሰላም አምላክ፥
20Bet miera Dievs, kas lielo avju Ganu, mūsu Kungu Jēzu Kristu, caur mūžīgās derības asinīm uzcēlis no miroņiem,
21በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን በእናንተ እያደረገ፥ ፈቃዱን ታደርጉ ዘንድ በመልካም ሥራ ሁሉ ፍጹማን ያድርጋችሁ፤ ለእርሱ እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።
21Lai stiprina jūs katrā labā darbā, ka jūs izpildītu Viņa gribu; lai Viņš jūsos padara to, kas Viņam patīk caur Jēzu Kristu, kam lai gods mūžīgi mūžos! Amen.
22ወንድሞች ሆይ፥ የምክርን ቃል እንድትታገሡ እመክራችኋለሁ፥ በጥቂት ቃል ጽፌላችኋለሁና።
22Bet es jūs, brāļi lūdzu: pieņemiet šos pamācības vārdus, jo es jums uzrakstīju tikai īsumā.
23ወንድማችን ጢሞቴዎስ እንደ ተፈታ እወቁ፥ ቶሎ ብሎም ቢመጣ ከእርሱ ጋር አያችኋለሁ።
23Ziniet, ka mūsu brālis Timotejs atbrīvots; kopā ar viņu (ja viņš drīz nāks) es jūs redzēšu.
24ለዋኖቻችሁ ሁሉና ለቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ አቅርቡልኝ። ከኢጣልያ የሆኑቱ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
24Sveiciniet visus savus priekšniekus un visus svētos! Jūs sveicina brāļi Itālijā.
25ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን፤ አሜን።
25Žēlastība ar jums visiem! Amen.