1Tātad, mani vismīļie brāļi, pēc kuriem es ļoti ilgojos, mans prieks un mans vainagojums, esiet pastāvīgi Kungā, jūs mīļie!
1ስለዚህ፥ የምወዳችሁና የምናፍቃችሁ፥ ደስታዬና አክሊሌ የምትሆኑ ወንድሞቼ ሆይ፥ እንዲሁ በጌታ ቁሙ፥ ወዳጆች ሆይ።
2Es lūdzu Evodiju un es lūdzu Sintihu būt vienprātīgām Kunga vārdā.
2በአንድ አሳብ በጌታ እንዲስማሙ ኤዎድያንን እመክራለሁ ሲንጤኪንንም እመክራለሁ።
3Arī tevi, mans īstais darba biedr, es lūdzu, palīdzi viņām, kas kopā ar mani, Klementu un citiem maniem palīgiem strādājušas evaņģēlija labā. Viņu vārdi ir ierakstīti dzīvības grāmatā.
3አንተም ደግሞ በሥራዬ አብረህ የተጠመድህ እውነተኛ ሆይ፥ እንድታግዛቸው እለምንሃለሁ፤ ስሞቻቸው በሕይወት መጽሐፍ ከተጻፉት ከቀሌምንጦስና ደግሞ ከእኔ ጋር አብረው ከሠሩት ከሌሎቹ ጋር በወንጌል ከእኔ ጋር አብረው ተጋድለዋልና።
4Priecājaties Kungā; es atkārtoti saku: priecājieties!
4ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።
5Jūsu laipnība lai ir zināma visiem cilvēkiem; Kungs ir tuvu,
5ገርነታችሁ ለሰው ሁሉ ይታወቅ።
6Neraizējieties ne par ko, bet jūsu lūgšanas un aizlūgumi lai nāk Dieva priekšā; visā pateicībā izsakiet savu vēlēšanos Viņam!
6ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።
7Un Dieva miers, kas pārspēj visu saprašanu, lai pasarga jūsu sirdis un jūsu domas Jēzū Kristū!
7አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።
8Beidzot, brāļi, kas ir patiess, kas godājams, kas taisnīgs, kas svēts, kas patīkams, kam laba slava, kas tikumīgs, kas cildināms, to domājiet!
8በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ እውነተኛ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ጭምትነት ያለበትን ነገር ሁሉ፥ ጽድቅ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ንጹሕ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ፍቅር ያለበትን ነገር ሁሉ፥ መልካም ወሬ ያለበትን ነገር ሁሉ፥ በጎነት ቢሆን ምስጋናም ቢሆን፥ እነዚህን አስቡ፤
9Un ko jūs mācījāties, un ko saņēmāt, un ko dzirdējāt, un ko pie manis redzējāt, to dariet! Un Dieva miers būs ar jums.
9ከእኔ የተማራችሁትንና የተቀበላችሁትን የሰማችሁትንም ያያችሁትንም እነዚህን አድርጉ፤ የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል።
10Bet es ļoti priecājos Kungā, ka jūs beigās atkal atplaukāt gādībā par mani, kā arī agrāk jau gādājāt, bet apstākļi jūs traucēja.
10ነገር ግን አሁን ከጊዜ በኋላ ስለ እኔ እንደ ገና ልታስቡ ስለ ጀመራችሁ፥ በጌታ እጅግ ደስ ይለኛል፤ ጊዜ አጣችሁ እንጂ፥ ማሰብስ ታስቡ ነበር።
11Ne trūkuma dēļ es to saku, jo esmu mācījies apmierināties ar to, kas man ir.
11ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና።
12Es protu pazemoties, protu arī pārpilnībā dzīvot (visur un pie visa kā esmu pieradis): būt paēdis un būt izsalcis, dzīvot pārpilnībā un ciest trūkumu,
12መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ።
13Es visu spēju Tanī, kas mani stiprina.
13ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።
14Tomēr jūs labi darījāt, dalīdamies ar mani manās bēdās.
14ሆኖም በመከራዬ ከእኔ ጋር ስለ ተካፈላችሁ መልካም አደረጋችሁ።
15Bet arī jūs, filipieši, ziniet, ka no evaņģēlija sludināšanas sākuma kā aizgāju no Maķedonijas, neviena draudze nav vienojusies ar mani došanā un ņemšanā, kā jūs vieni.
15የፊልጵስዩስ ሰዎች ሆይ፥ ወንጌል በመጀመሪያ ሲሰበክ፥ ከመቄዶንያ በወጣሁ ጊዜ፥ ከእናንተ ብቻ በቀር ሌላ ቤተ ክርስቲያን በመስጠትና በመቀበል ስሌት ከእኔ ጋር እንዳልተካፈለች እናንተ ደግሞ ታውቃላችሁ፤
16Jo arī uz Tesalonīki jūs sūtījāt vienreiz un otrreiz to, kas man bija vajadzīgs.
16በተሰሎንቄ እንኳ ሳለሁ፥ አንድ ጊዜና ሁለት ጊዜ ያስፈለገኝን ሰዳችሁልኝ ነበርና።
17Ne it kā es meklētu dāvanas, bet es meklēju ieguvumu, kas vairotos jums par labu.
17በስሌታችሁ የሚበዛውን ፍሬ እንጂ ስጦታውን ፈላጊ አይደለሁም።
18Man viss ir un ir pārpilnībā. Saņēmis no Epafrodīta to, ko jūs sūtījāt, šo saldo smaržu, Dievam pieņemamo un patīkamo upuri, es esmu nodrošināts.
18ነገር ግን ሁሉ አለኝ ይበዛልኝማል፤ የመዓዛ ሽታና የተወደደ መሥዋዕት የሚሆነውን ለእግዚአብሔርም ደስ የሚያሰኘውን ስጦታችሁን ከአፍሮዲጡ ተቀብዬ ተሞልቼአለሁ።
19Bet mans Dievs savā bagātībā lai piepilda visas jūsu vēlēšanās Jēzus Kristus godībā!
19አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሞላባችኋል።
20Dievam un mūsu Tēvam lai gods mūžīgi mūžos! Amen.
20ለአምላካችንና ለአባታችንም እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።
21Sveiciniet ikvienu svēto Kristū Jēzū!
21ለቅዱሳን ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ሰላምታ አቅርቡ። ከእኔ ጋር ያሉቱ ወንድሞች ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
22Jūs sveicina brāļi, kas pie manis. Jūs sveicina visi svētie, bet sevišķi tie, kas no ķeizara nama.
22ቅዱሳን ሁሉ ይልቁንም ከቄሣር ቤት የሆኑቱ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
23Mūsu Kunga Jēzus Kristus žēlastība lai ir ar jūsu garu! Amen.
23የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን፤ አሜን።