1Brāļi, manas sirds vēlēšanās un aizlūgums pie Dieva ir par viņiem, lai viņi tiktu pestīti.
1ወንድሞች ሆይ፥ የልቤ በጎ ፈቃድና ስለ እስራኤል ወደ እግዚአብሔር ልመናዬ እንዲድኑ ነው።
2Jo es viņiem liecinu, ka viņiem ir centība uz Dievu, bet nav izpratnes.
2በእውቀት አይቅኑ እንጂ ለእግዚአብሔር እንዲቀኑ እመሰክርላቸዋለሁና።
3Pārprazdami Dieva taisnību un cenzdamies nostiprināt savu, viņi nepakļāvās Dieva taisnībai.
3የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።
4Jo likuma gala mērķis ir Kristus, kas katram ticīgajam sagādā attaisnojumu.
4የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና።
5Jo Mozus raksta: katrs cilvēks, kas izpildīs likuma taisnību, dzīvos tanī.
5ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና።
6Bet taisnība, kas nāk no ticības, saka tā: Nesaki savā sirdī: kas uzkāps debesīs, tas ir, lai novestu Kristu,
6ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል። በልብህ። ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤
7Vai arī: kas nokāps bezdibenī, tas ir, lai atsauktu Kristu no miroņiem!
7ወይም። በልብህ። ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።
8Bet ko saka Raksti? Vārds ir tuvu, tavā mutē un tavā sirdī; tas ir ticības vārds, ko mēs sludinām.
8ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።
9Jo, ja tu ar savu muti atzīsi Kungu Jēzu un savā sirdī ticēsi, ka Dievs Viņu uzmodinājis no miroņiem, tad būsi pestīts.
9ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
10Jo sirdī ticam, lai panāktu attaisnošanu, bet ar muti apliecinām, lai panāktu pestīšanu.
10ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
11Jo Raksti saka: Katrs, kas uz Viņu tic, nepaliks kaunā. (Is.28,16)
11መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
12Un nav izšķirības starp jūdu un grieķi, jo tas pats Kungs pār visiem, bagāts visiem, kas Viņu piesauc.
12በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
13Jo katrs, kas piesauks Kunga vārdu, tiks pestīts. (Jl.2,32; Apd.2,21)
13የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
14Bet kā tie piesauks to, kam nav ticējuši? Vai kā lai tic uz to, par ko nav dzirdējuši? Bet kā lai dzird bez sludinātāja?
14እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?
15Bet kā lai sludina bez sūtības? Ir rakstīts: Cik tīkamas to kājas, kas sludina mieru, kas sludina labu!
15መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ?
16Bet ne visi ir paklausīgi evaņģēlijam. Jo Isajs saka: Kungs, kas ir ticējis tam, ko no mums dzirdējis?
16ነገር ግን ሁሉ ለምሥራቹ ቃል አልታዘዙም። ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ምስክርነታችንን ማን አመነ? ብሎአልና።
17Tātad ticība nāk no dzirdēšanas, bet dzirdētais - caur Kristus vārdu.
17እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።
18Bet es saku: Vai viņi nav dzirdējuši? Un taču pār visu zemi ir atskanējusi viņu balss un līdz zemeslodes robežām viņu vārdi. (Ps 18)
18ዳሩ ግን። ባይሰሙ ነው ወይ? እላለሁ። በእውነት። ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።
19Bet es jautāju: Vai Izraēlis nesaprata? Mozus pirmais saka: Es jūs novedīšu līdz skaudībai pret vienu netautu, es jūs ievedīšu dusmās pret nesaprātīgu tautu. (5 Moz 32,21)
19ነገር ግን። እስራኤል ባያውቁ ነው ወይ? እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ። እኔ ሕዝብ በማይሆነው አስቀናችኋለሁ በማያስተውልም ሕዝብ አስቆጣችኋለሁ
20Bet Isajs uzdrošinās sacīt: Tie, kas mani nemeklēja, atrada mani; es atklāti parādījos tiem, kas pēc manis nevaicāja. (Is 65,1)
20ብሎአል። ኢሳይያስም ደፍሮ። ላልፈለጉኝ ተገኘሁ፥ ላልጠየቁኝም ተገለጥሁ አለ።
21Bet Izraēlim viņš saka: Augu dienu es stiepu savas rokas pretim neticīgai un stūrgalvīgai tautai. (Is 65,2)
21ስለ እስራኤል ግን። ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ ይላል።