1Tātad es jautāju: Vai Dievs savu tautu ir atmetis? - Nekādā ziņā; jo arī es esmu izraēlietis, Ābrahama pēcnācējs, no Benjamīna cilts.
1እንግዲህ። እግዚአብሔር ሕዝቡን ጣላቸውን? እላለሁ። አይደለም እኔ ደግሞ እስራኤላዊና ከአብርሃም ዘር ከብንያምም ወገን ነኝና።
2Dievs nav atmetis savu tautu, kuru Viņš iepriekš bija izredzējis. Vai jūs nezināt, ko Raksti saka par Eliju, kā viņš žēlojās Dievam par Izraēli?
2እግዚአብሔር አስቀድሞ ያወቃቸውን ሕዝብ አልጣላቸውም። መጽሐፍ ስለ ኤልያስ በተጻፈው የሚለውን፥ በእግዚአብሔር ፊት እስራኤልን እንዴት እንደሚከስ፥ አታውቁምን?
3Kungs, tie nogalināja Tavus praviešus, viņi nopostīja Tavus altārus, un es esmu viens atlicis, un viņi tiecas pēc manas dzīvības.
3ጌታ ሆይ፥ ነቢያትህን ገደሉ መሠዊያዎችህንም አፈረሱ እኔም ብቻዬን ቀረሁ ነፍሴንም ይሹአታል።
4Bet ko saka viņam Dieva atbilde? - Es atstāju sev septiņus tūkstošus vīru, kas savus ceļus nav locījuši Baala priekšā.
4ነገር ግን አምላካዊ መልስ ምን አለው? ለበአል ያልሰገዱትን ሰባት ሺህ ሰዎች ለእኔ አስቀርቼአለሁ።
5Tā arī šinī laikā izglābts ir atlikums saskaņā ar žēlastības izvēli.
5እንደዚሁም በአሁን ዘመን ደግሞ በጸጋ የተመረጡ ቅሬታዎች አሉ።
6Bet ja no žēlastības, tad jau ne darbu dēļ, citādi žēlastība nebūtu žēlastība.
6በጸጋ ከሆነ ግን ከሥራ መሆኑ ቀርቶአል፤ ጸጋ ያለዚያ ጸጋ መሆኑ ቀርቶአል።
7Kā tad ir? - Pēc kā tiecās Izraēlis, to viņš nav sasniedzis, tikai izredzētie to sasniedza, bet pārējie palika apstulbināti,
7እንግዲህ ምንድር ነው? እስራኤል የሚፈልጉትን አላገኙትም፤ የተመረጡት ግን አገኙት፤
8Kā rakstīts: Dievs deva viņiem truluma garu: acis, lai neredzētu, un ausis, lai nedzirdētu līdz pat šai dienai.
8ሌሎቹም ደነዘዙ፤ እንዲሁም። ዓይኖቻቸው እንዳያዩ ጆሮቻቸውም እንዳይሰሙ እግዚአብሔር የእንቅልፍ መንፈስን እስከ ዛሬ ድረስ ሰጣቸው ተብሎ ተጽፎአል። ዳዊትም።
9Un Dāvids saka: Viņu galds lai tiem kļūst par slazdu un cilpu, un apgrēcību, un atmaksu.
9ማዕዳቸው ወጥመድና አሽክላ ማሰናከያም ፍዳም ይሁንባቸው፤
10Viņu acis lai tiek aptumšotas, ka tie neredzētu, un viņu muguras liec vienmēr!
10ዓይኖቻቸው እንዳያዩ ይጨልሙ፥ ጀርባቸውንም ዘወትር አጉብጥ ብሎአል።
11Tātad es jautāju: Vai viņi tā klupuši, lai kristu? Nekādā ziņā; bet viņu grēka dēļ pestīšana nākusi pagāniem, lai viņi ar tiem sacenstos.
11እንግዲህ። የተሰናከሉ እስኪወድቁ ድረስ ነውን? እላለሁ። አይደለም፤ ነገር ግን እነርሱን ያስቀናቸው ዘንድ በእነርሱ በደል መዳን ለአሕዛብ ሆነ።
12Bet ja viņu grēks ir pasaulei bagātība, un viņu mazais skaits pagāniem ieguvums, tad jo vairāk viņu pilnskaits.
12ዳሩ ግን በደላቸው ለዓለም ባለ ጠግነት መሸነፋቸውም ለአሕዛብ ባለ ጠግነት ከሆነ፥ ይልቁንስ መሙላታቸው እንዴት ይሆን?
13Un jums, pagāniem, es saku: Kamēr es esmu pagānu apustulis, es savu kalpošanu pagodināšu,
13ለእናንተም ለአሕዛብ እናገራለሁ። እኔ የአሕዛብ ሐዋርያ በሆንሁ መጠን ሥጋዬ የሆኑትን አስቀንቼ ምናልባት ከእነርሱ አንዳንዱን አድን እንደሆነ አገልግሎቴን አከብራለሁ።
14Kaut kādā veidā pamudinādams savus ciltsbrāļus uz sacensību un dažus no viņiem izglābdams.
15የእነርሱ መጣል ለዓለም መታረቅ ከሆነ ከሙታን ከሚመጣ ሕይወት በቀር መመለሳቸው ምን ይሆን?
15Ja jau viņu atmešana ir izlīdzināšana pasaulei, kas tad būs pieņemšana, ja ne atdzīvināšana no mirušiem?
16በኵራቱም ቅዱስ ከሆነ ብሆው ደግሞ ቅዱስ ነው፤ ሥሩም ቅዱስ ከሆነ ቅርንጫፎቹ ደግሞ ቅዱሳን ናቸው።
16Ja pirmupuris ir svēts, tad arī visa mīkla, un ja sakne ir svēta, tad arī zari.
17ነገር ግን ከቅርንጫፎች አንዳንዱ ቢሰበሩ አንተም የበረሀ ወይራ የሆንህ በመካከላቸው ገብተህ ከእነርሱ ጋር የወይራ ዘይት ከሚወጣው ሥር ተካፋይ ከሆንህ፥ በቅርንጫፎች ላይ አትመካ፤
17Bet ja daži zari nolauzti un tu, meža olīvkoka atvase, esi uzpotēta to vietā un esi kļuvusi olīvkoka saknes un sulas līdzdalībniece,
18ብትመካባቸው ግን ሥሩ አንተን ይሸከምሃል እንጂ ሥሩን የምትሸከም አንተ አይደለህም።
18Tad nelielies zaru priekšā! Bet ja lielies, tad zini, ka ne tu nes sakni, bet sakne tevi!
19እንግዲህ። እኔ እንድገባ ቅርንጫፎች ተሰበሩ ትል ይሆናል።
19Tu varbūt sacīsi: Zari tika nolauzti, lai mani uzpotētu.
20መልካም፤ እነርሱ ከአለማመን የተነሣ ተሰበሩ አንተም ከእምነት የተነሣ ቆመሃል። ፍራ እንጂ የትዕቢትን ነገር አታስብ።
20Labi! Tie nolauzti neticības dēļ, bet tu stāvi, pateicoties ticībai; neesi augstprātīgs, bet bijīgs!
21እግዚአብሔር እንደ ተፈጠሩት ለነበሩት ቅርንጫፎች የራራላቸው ካልሆነ ለአንተ ደግሞ አይራራልህምና።
21Jo ja Dievs nav saudzējis dabiskos zarus, tad taču arī tevi nesaudzēs.
22እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ጭከና ተመልከት፤ ጭከናው በወደቁት ላይ ነው፥ በቸርነቱ ግን ጸንተህ ብትኖር የእግዚአብሔር ቸርነት በአንተ ላይ ነው፤ ያለዚያ አንተ ደግሞ ትቆረጣለህ።
22Tāpēc vēro Dieva labumu un bardzību: bardzību pret tiem, kas krituši, bet pret sevi Dieva labumu, ja tu labajā pastāvēsi, citādi arī tevi nocirtīs.
23እነዚያም ደግሞ በአለማመናቸው ጸንተው ባይኖሩ በዛፉ ውስጥ ይገባሉ፤ እግዚአብሔር መልሶ ሊያገባቸው ይችላልና።
23Bet arī tie tiks uzpotēti, ja viņi nepaliks savā neticībā, jo Dievs ir spējīgs viņus atkal uzpotēt.
24አንተ በፍጥረቱ የበረሀ ከነበረ ወይራ ተቆርጠህ እንደ ፍጥረትህ ሳትሆን በመልካም ወይራ ከገባህ፥ ይልቁንስ እነዚያ በፍጥረታቸው ያሉት ቅርንጫፎች በራሳቸው ወይራ እንዴት አይገቡም?
24Jo ja tu esi nocirsts no meža olīvkoka, kam pēc dabas piederi, un pret dabu uzpotēts labajam olīvkokam, tad jo vairāk tie, kas attiecīgi savai dabai tiek uzpotēti savam olīvkokam.
25ወንድሞች ሆይ፥ ልባሞች የሆናችሁ እንዳይመስላችሁ ይህን ምሥጢር ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ፤ የአሕዛብ ሙላት እስኪገባ ድረስ ድንዛዜ በእስራኤል በአንዳንድ በኩል ሆነባቸው፤
25Bet es jūs, brāļi, negribu atstāt neziņā par šo noslēpumu (lai jūs nekļūtu iedomīgi), ka viena Izraēļa daļa skarta ar aklumu, līdz kamēr tautu visums būs iegājis.
26እንደዚሁም እስራኤል ሁሉ ይድናል፤ እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ። መድኃኒት ከጽዮን ይወጣል ከያዕቆብም ኃጢአተኛነትን ያስወግዳል።
26Un tā viss Izraēlis tiktu glābts, kā rakstīts: No Siona nāks Glābējs un novērsīs bezdievību no Jēkaba.
27ኃጢአታቸውንም ስወስድላቸው ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው።
27Un šī ir mana derība ar viņiem, ka es piedošu viņu grēkus. (Is.59,20)
28በወንጌልስ በኩል ስለ እናንተ ጠላቶች ናቸው፥ በምርጫ በኩል ግን ስለ አባቶች ተወዳጆች ናቸው፤
28Attiecībā uz evaņģēliju viņi ir ienaidnieki jūsu dēļ, bet kas attiecas uz izredzēšanu, viņi ir vismīļie sentēvu dēļ.
29እግዚአብሔር በጸጋው ስጦታና በመጥራቱ አይጸጸትምና።
29Jo žēlastības dāvanas un aicinājumu Dievs nenožēlo.
30እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር እንዳልታዘዛችሁ፥ አሁን ግን ከአለመታዘዛቸው የተነሣ ምሕረት እንዳገኛችሁ፥
30Jo kā arī jūs kādreiz neticējāt Dievam, bet tagad esat ieguvuši žēlsirdību viņu neticības dēļ,
31እንዲሁ በተማራችሁበት ምሕረት እነርሱ ደግሞ ምሕረትን ያገኙ ዘንድ እነዚህ ደግሞ አሁን አልታዘዙም።
31Tā arī viņi neticēja jūsu apžēlošanai, lai paši iegūtu apžēlošanu.
32እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን በአለመታዘዝ ዘግቶታልና።
32Jo Dievs visu ieslēdzis neticībā, lai visus apžēlotu.
33የእግዚአብሔር ባለ ጠግነትና ጥበብ እውቀቱም እንዴት ጥልቅ ነው፤ ፍርዱ እንዴት የማይመረመር ነው፥ ለመንገዱም ፍለጋ የለውም።
33Ak, kāds ir Dieva gudrības un zināšanas bagātību dziļums! Cik neizprotami ir Viņa lēmumi un neizdibināmi Viņa ceļi!
34የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው?
34Jo kas gan ir izpratis Dieva prātu, vai kas bijis Viņa padomdevējs?
35ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው?
35Vai kas Viņam iepriekš ko devis, lai saņemtu atlīdzinājumu?
36ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።
36Jo no Viņa un caur Viņu, un Viņā ir viss. Viņam lai gods mūžīgi! Amen.