1Tāpēc, brāļi, Dieva žēlsirdības dēļ es jūs lūdzu: nododiet savas miesas par dzīvu, svētu, Dievam patīkamu upuri, lai tas būtu jūsu garīgais dievkalpojums!
1እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው።
2Un nepiemērojieties šai pasaulei, bet pārvērtieties, atjaunodamies savā garā, lai jūs saprastu, kāds ir Dieva prāts, kas labs un patīkams, un pilnīgs!
2የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።
3Jo, pateicoties žēlastībai, kas man dota, es visiem starp jums saku: Nedomājiet par sevi augstāk, nekā pienākas domāt, bet domājiet saprātīgi saskaņā ar to ticības mēru, kādu katram Dievs piešķīris.
3እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ የእምነትን መጠን እንዳካፈለው፥ እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ጸጋ እናገራለሁ።
4Un kā mūsu ķermenī ir daudz locekļu, bet ne visiem locekļiem tas pats uzdevums,
4በአንድ አካል ብዙ ብልቶች እንዳሉን፥ የብልቶቹም ሁሉ ሥራ አንድ እንዳይደለ፥
5Tāpat mēs daudzi esam viens ķermenis Kristū, bet atsevišķi mēs esam viens otra locekļi.
5እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን፥ እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን።
6Bet mums ir dāvanas, kas mums dotas attiecīgi žēlastībai, un tās ir dažādas: paraviešu dāvanas, kuras izmantojamas saskaņā ar ticību,
6እንደ ተሰጠንም ጸጋ ልዩ ልዩ ስጦታ አለን፤ ትንቢት ቢሆን እንደ እምነታችን መጠን ትንቢት እንናገር፤
7Kalpošanas pienākums, kas jāpilda kalpojot, mācīšanas - mācot;
7አገልግሎት ቢሆን በአገልግሎታችን እንትጋ፤ የሚያስተምርም ቢሆን በማስተማሩ ይትጋ፤
8Kas sludinātājs, lai sludina, kas dala dāvanas, lai dara to vientiesīgi, kas ir priekšnieks, lai pilda rūpīgi, kas strādā žēsirdības darbu, lai dara to ar prieku!
8የሚመክርም ቢሆን በመምከሩ ይትጋ፤ የሚሰጥ በልግስና ይስጥ፤ የሚገዛ በትጋት ይግዛ፤ የሚምር በደስታ ይማር።
9Mīlestībai jābūt neliekuļotai. Nīzdami ļaunu, pastāviet labajā!
9ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን። ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤
10Brāļu mīlestībā mīliet viens otru, godbijībā pārsteidziet cits citu!
10በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤
11Neesiet kūtri centībā, esiet dedzīgi garā, kalpojiet Kungam!
11ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤
12Esiet priecīgi cerībā, pacietīgi bēdās, pastāvīgi lūgšanā!
12በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤
13Ņemiet līdzdalību svēto vajadzībās, centieties būt viesmīlīgi!
13ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ።
14Svētiet tos, kas jūs vajā, svētiet, bet nelādiet!
14የሚያሳድዱአችሁን መርቁ፥ መርቁ እንጂ አትርገሙ።
15Priecājieties ar priecīgajiem, raudiet ar tiem, kas raud!
15ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።
16Esiet savstarpēji vienprātīgi! Neesiet augstprātīgi, bet pazemojieties ar pazemīgajiem! Neesiet pārgudri paši sevī!
16እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ፤ የትዕቢትን ነገር አታስቡ፥ ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ። ልባሞች የሆናችሁ አይምሰላችሁ።
17Nevienam ļaunu ar ļaunu neatmaksādami, sekmējiet labu nevien Dievam, bet arī visu cilvēku priekšā!
17ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ።
18Ja iespējams, ieturiet mieru ar visiem cilvēkiem, cik tas no jums atkarīgs!
18ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።
19Vismīļie, neatriebieties jūs paši, bet dodiet vietu dusmām, par kurām rakstīts: Man pieder atriebšana, es atmaksāšu, saka Kungs.
19ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።
20Bet ja tavs ienaidnieks ir izsalcis, paēdini viņu, ja viņš cieš slāpes, dod viņam dzert! To darīdams, tu sakrāsi uz viņa galvas kvēlojošas ogles.
20ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና።
21Ļaunums nedrīkst tevi uzvarēt, bet tu uzvari ļaunumu ar labu!
21ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።