Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Romans

13

1Katrs cilvēks lai ir padots priekšniecības varai, jo nav varas, kā tikai no Dieva; un tā, kas ir, ir Dieva iecelta.
1ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው።
2Tāpēc, kas pretojas priekšniecībai, pretojas Dieva rīcībai; bet tie, kas pretojas, paši sev sagādā pazudināšanu.
2ስለዚህ ባለ ሥልጣንን የሚቃወም የእግዚአብሔርን ሥርዓት ይቃወማል፤ የሚቃወሙትም በራሳቸው ላይ ፍርድን ይቀበላሉ።
3Jo priekšnieki nav atbaidīšanai no laba, bet no ļauna. Bet ja tu gribi, ka tev priekšniecības nevajadzētu bīties, dari labu un tu saņemsi tās uzslavu,
3ገዥዎች ለክፉ አድራጊዎች እንጂ መልካም ለሚያደርጉ የሚያስፈሩ አይደሉምና። ባለ ሥልጣንን እንዳትፈራ ትወዳለህን? መልካሙን አድርግ ከእርሱም ምስጋና ይሆንልሃል፤
4Jo tā ir Dieva kalpone tavā labā. Bet ja tu dari ļaunu, tad bīsties, jo velti tā zobenu nenēsā. Viņa ir Dieva kalpone, atriebēja tā sodīšanai, kas dara ļaunu.
4ለመልካም ነገር ለአንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና። በከንቱ ግን ሰይፍ አይታጠቅምና ክፉ ብታደርግ ፍራ፤ ቍጣውን ለማሳየት ክፉ አድራጊውን የሚበቀል የእግዚአብሔር አገልጋይ ነውና።
5Tātad nepieciešami esiet paklausīgi ne tikai soda dēļ, bet arī sirdsapziņas dēļ.
5ስለዚህ ስለ ቍጣው ብቻ አይደለም ነገር ግን ስለ ሕሊና ደግሞ መገዛት ግድ ነው።
6Tāpēc jūs arī maksājat nodokļus, jo viņi, būdami Dieva kalpi, kalpo šim nolūkam.
6ስለዚህ ደግሞ ትገብራላችሁና፤ በዚህ ነገር የሚተጉ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸውና።
7Tātad atdodiet katram, kas kam pienākas: nodokli, kam pienākas nodoklis; muitu, kam pienākas muita; bijību, kam nākas bijība; godu, kam nākas gods!
7ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ግብር ለሚገባው ግብርን፥ ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን፥ መፈራት ለሚገባው መፈራትን፥ ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ።
8Nepalieciet nevienam nekā parādā, kā tikai savstarpējo mīlestību, jo, kas mīl savu tuvāko, tas izpilda likumu.
8እርስ በርሳችሁ ከመዋደድ በቀር ለማንም ዕዳ አይኑርባችሁ፥ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈጽሞታልና።
9Jo: tev nebūs laulību pārkāpt, tev nebūs nokaut, tev nebūs zagt, tev nebūs nepatiesu liecību dot, tev nebūs iekārot, kā arī visi citi baušļi ir ietverti šajos vārdos: Tev būs mīlēt savu tuvāko kā sevi pašu!
9አታመንዝር፥ አትግደል፥ አትስረቅ፥ በውሸት አትመስክር፥ አትመኝ የሚለው ከሌላይቱ ትእዛዝ ሁሉ ጋር በዚህ። ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ በሚለው ቃል ተጠቅልሎአል።
10Mīlestība nedara tuvākajam ļaunu. Tātad bauslības piepildījums ir mīlestība.
10ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው።
11Un izprotiet šo laiku, jo mums jau pienākusi stunda celties no miega; un mūsu pestīšana tagad ir tuvāk nekā tad, kad kļuvām ticīgi.
11ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።
12Nakts ir pagājusi, diena iestājusies; tāpēc atmetīsim tumsības darbus un ietērpsimies gaismas bruņās!
12ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ።
13Dzīvosim godīgi kā dienā: ne plītēdami un dzīrodami, ne izvirtībā un netiklībā, ne ķildās un skaudībā,
13በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤
14Bet ietērpieties Kungā Jēzū Kristū! Arī miesu nelutiniet kārībām!
14ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ።