1Pieņemiet vājos ticībā, neķildojieties par uzsaktu dažādību!
1በእምነት የደከመውንም ተቀበሉት፥ በአሳቡም ላይ አትፍረዱ።
2Jo dažs ir pārliecināts, ka viņam brīv visu ēst, turpretī vājais lai ēd dārzājus.
2ሁሉን ይበላ ዘንድ እንደ ተፈቀደለት የሚያምን አለ፥ ደካማው ግን አትክልት ይበላል።
3Tas, kas ēd, lai nenicina to, kas neēd, bet tas, kas neēd, lai netiesā ēdāju, jo Dievs viņu pieņēmis.
3የሚበላ የማይበላውን አይናቀው የማይበላውም በሚበላው አይፍረድ፥ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና።
4Kas tu esi, ka tu tiesā cita kalpu? Viņš stāv un krīt par savu Kungu; un viņš stāvēs, jo Dievs ir spējīgs viņu nostiprināt.
4አንተ በሌላው ሎሌ የምትፈርድ ማን ነህ? እርሱ ቢቆም ወይም ቢወድቅ ለገዛ ጌታው ነው፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊያቆመው ይችላልና ይቆማል።
5Jo dažš šķiro dienu no dienas, citam visas dienas ir vienādas; katrs lai paliek savā pārliecībā!
5ይህ ሰው አንድ ቀን ከሌላ ቀን እንዲሻል ያስባል፥ ያ ግን ቀን ሁሉ አንድ እንደ ሆነ ያስባል፤ እያንዳንዱ በገዛ አእምሮው አጥብቆ ይረዳ።
6Kas šķiro dienas, tas Kungam tās šķiro; un kas ēd, tas ēd Kunga dēļ un pateicas Dievam. Arī tas, kas neēd, neēd Kunga dēļ un arī pateicas Dievam.
6ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል፤ የሚበላም እግዚአብሔርን ያመሰግናልና ለጌታ ብሎ ይበላል፤ የማይበላም ለጌታ ብሎ አይበላም እግዚአብሔርንም ያመሰግናል።
7Jo neviens no mums nedzīvo sev, un neviens nemirst sev.
7ከእኛ አንድ ስንኳ ለራሱ የሚኖር የለምና፥ ለራሱም የሚሞት የለም፤
8Ja tad mēs dzīvojam, dzīvojam Kungam, ja mirstam, mirstam Kungam. Tātad, vai mēs dzīvojam, vai mirstam, mēs piederam Kungam.
8በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፥ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን። እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን።
9Jo tāpēc Kristus nomira un augšāmcēlās, lai valdītu pār mirušajiem un dzīvajiem.
9ስለዚህ ነገር ሙታንንም ሕያዋንንም ይገዛ ዘንድ ክርስቶስ ሞቶአልና ሕያውም ሆኖአልና።
10Bet kāpēc tu tiesā savu brāli? Vai kāpēc tu nicini savu brāli? Mēs visi taču stāsimies Kristus soģa krēsla priekšā.
10አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና።
11Jo ir rakstīts: Tik tiešām, ka es dzīvoju, saka Kungs, visi ceļi tiks locīti manā priekšā, un ikviena mēle atzīs Dievu. (Is.45,23-24)
11እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና።
12Tātad katrs no mums dos Dievam norēķinu par sevi.
12እንግዲያስ እያንዳንዳችን ስለ ራሳችን ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።
13Tāpēc netiesāsim vairs viens otru, bet labāk apsveriet to, lai nedotu savam brālim piedauzību vai apgrēcību.
13እንግዲህ ከዛሬ ጀምሮ እርስ በርሳችን አንፈራረድ፤ ይልቁን ግን ለወንድም እንቅፋትን ወይም ማሰናከያን ማንም እንዳያኖርበት ይህን ቍረጡ።
14Es zinu un es esmu pārliecināts Kungā Jēzū, ka pats par sevi nekas nav nešķīsts; tikai tam ir nešķīsts, kas ko par nešķīstu uzskata.
14በራሱ ርኵስ የሆነ ነገር እንደ ሌለ በጌታ በኢየሱስ ሆኜ አውቄአለሁ ተረድቼአለሁም፤ ነገር ግን ምንም ርኵስ እንዲሆን ለሚቆጥር ለእርሱ ርኵስ ነው።
15Jo ja tavs brālis ēdiena dēļ tiek apbēdināts, tad tu vairs nedzīvo mīlestībā. Nepazudini ēdiena dēļ to, kura dēļ Kristus ir miris!
15ወንድምህንም በመብል ምክንያት የምታሳዝን ከሆንህ እንግዲህ በፍቅር አልተመላለስህም። ክርስቶስ ስለ እርሱ የሞተለትን እርሱን በመብልህ አታጥፋው።
16Tātad, lai netiek zaimots tas, kas mums ir labs!
16እንግዲህ ለእናንተ ያለው መልካም ነገር አይሰደብ፤
17Jo ne ēšana un dzeršana ir Dieva valstība, bet taisnība un miers, un prieks Svētajā Garā.
17የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና።
18Jo kas šinīs lietās kalpo Kristum, tas ir patīkams Dievam un pieņemams cilvēkiem.
18እንደዚህ አድርጎ ለክርስቶስ የሚገዛ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛልና፥ በሰውም ዘንድ የተመሰገነ ነው።
19Tāpēc centīsimies pēc tā, kas veicina mieru, un savstarpēji sargāsim to, kas mūs ceļ!
19እንግዲያስ ሰላም የሚቆምበትን እርስ በርሳችንም የምንታነጽበትን እንከተል።
20Neposti Dieva darbu ēdiena dēļ! Viss gan ir šķīsts, bet cilvēkam, kas ēd un apgrēcinās, tas ir par ļaunu.
20በመብል ምክንያት የእግዚአብሔርን ሥራ አታፍርስ። ሁሉ ንጹሕ ነው፥ በመጠራጠር የተበላ እንደ ሆነ ግን ለዚያ ሰው ክፉ ነው።
21Labi ir neēst gaļu un nedzert vīnu, un nedarīt neko citu, kas dod piedauzību tavam brālim, to apgrēcina vai padara viņu vāju.
21ሥጋን አለመብላት ወይንንም አለመጠጣት ወንድምህም የሚሰናከልበትን አለማድረግ መልካም ነው።
22Ja tev ir pārliecība, tad paturi to pie sevis Dieva priekšā! Svētīgs ir tas, kas sev nepārmet par to, ko atzīst par labu.
22ለአንተ ያለህ እምነት በእግዚአብሔር ፊት ለራስህ ይሁንልህ። ፈትኖ መልካም እንዲሆን በሚቈጥረው ነገር በራሱ ላይ የማይፈርድ ብፁዕ ነው።
23Bet tas, kas šaubīdamies ēd, ir notiesāts, tāpēc ka to nedara aiz pārliecības; jo viss, kas nenāk no pārliecības ir grēks.
23የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው።