1Un es jums ieteicu Fēbu, mūsu māsu, kas kalpo Kenhrejas baznīcā.
1በክንክራኦስ ባለች ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የምትሆን እኅታችንን ፌቤንን አደራ ብያችኋለሁ፤
2Uzņemiet viņu Kunga vārdā, kā tas svētajiem piederas, un izpalīdziet visur, kur viņai jūsu palīdzība būs vajadzīga, jo arī viņa palīdz daudziem un arī man!
2ለቅዱሳን እንደሚገባ በጌታ ተቀበሉአት፥ እርስዋ ለብዙዎች ለእኔም ለራሴ ደጋፊ ነበረችና፥ ከእናንተም በምትፈልገው በማናቸውም ነገር እርዱአት።
3Kristū Jēzū sveiciniet manus palīgus, Prisku un Akvilu,
3በክርስቶስ ኢየሱስ አብረውኝ ለሚሠሩ ለጵርስቅላና ለአቂላ ሰላምታ አቅርቡልኝ፤
4(Kuri par manu dzīvību ķīlā likuši savas galvas. Viņiem nevien es esmu pateicīgs, bet arī visas pagānu draudzes.)
4እነርሱም ስለ ነፍሴ ነፍሳቸውን ለሞት አቀረቡ፥ የአሕዛብም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የሚያመሰግኑአቸው ናቸው እንጂ እኔ ብቻ አይደለሁም፤
5Un arī viņu mājas draudzi! Sveiciniet manu mīļo Epenetu, kas Āzijā ir pirmdzimtais Kristū!
5በቤታቸውም ላለች ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ አቅርቡልኝ። ከእስያ ለክርስቶስ በኵራት ለሆነው ለምወደው ለአጤኔጦን ሰላምታ አቅርቡልኝ።
6Sveiciniet Mariju, kas daudz strādājusi jūsu labā!
6ስለ እናንተ ብዙ ለደከመች ለማርያ ሰላምታ አቅርቡልኝ።
7Sveiciniet Andronīku un Jūniju, manus tuviniekus un cietuma biedrus, kas ir cieņā starp apustuļiem un jau pirms manis piederēja Kristum!
7በሐዋርያት መካከል ስመ ጥሩዎች ለሆኑ፥ ደግሞም ክርስቶስን በማመን ለቀደሙኝ፥ አብረውኝም ለታሰሩ ለዘመዶቼ ለአንዲራኒቆንና ለዩልያን ሰላምታ አቅርቡልኝ።
8Sveiciniet Ampliatu, kas man mīļš Kungā!
8በጌታ ለምወደው ለጵልያጦን ሰላምታ አቅርቡልኝ።
9Sveiciniet Urbānu, mūsu palīgu Kristū Jēzū, un manu mīļo Stahiju!
9በክርስቶስ አብሮን ለሚሠራ ለኢሩባኖን ለምወደውም ለስንጣክን ሰላምታ አቅርቡልኝ።
10Sveiciniet Kristū pārbaudīto Apellu!
10በክርስቶስ መሆኑ ተፈትኖ ለተመሰገነው ለኤጤሌን ሰላምታ አቅርቡልኝ። ከአርስጣባሉ ቤተ ሰዎች ላሉት ሰላምታ አቅርቡልኝ።
11Aristobūla mājas iemitniekus! Sveiciniet manu radinieku Herodionu! Sveiciniet Narkisa mājas ļaudis, kas pieder Kungam!
11ለዘመዴ ለሄሮድዮና ሰላምታ አቅርቡልኝ። ከንርቀሱ ቤተ ሰዎች በጌታ ላሉት ሰላምታ አቅርቡልኝ።
12Sveiciniet Trifenu un Trifozu, kas strādā Kungam! Sveiciniet dārgo Persidi, kas daudz strādājusi Kungā!
12በጌታ ሆነው ለሚደክሙ ለፕሮፊሞናና ለጢሮፊሞሳ ሰላምታ አቅርቡልኝ። በጌታ እጅግ ለደከመች ለተወደደች ለጠርሲዳ ሰላምታ አቅርቡልኝ።
13Sveiciniet Rufu, Kunga izredzēto, un viņa un manu māti!
13በጌታ ሆኖ ለታወቀ ለሩፎን ለእኔና ለእርሱም እናት ሰላምታ አቅርቡልኝ።
14Sveiciniet Asinkritu, Flegontu, Hermeju, Patrobu, Hermu un brāļus, kas ar viņiem ir!
14ለአስቀሪጦንና ለአፍለሶንጳ ለሄሮሜንም ለጳጥሮባም ለሄርማንም ከእነርሱም ጋር ላሉ ወንድሞች ሰላምታ አቅርቡልኝ።
15Sveiciniet Filologu un Jūliju, Nēreju un viņa māsu, un Olimpiju, un visus svētos, kas ir kopā ar viņiem!
15ለፍሌጎንና ለዩልያ ለኔርያና ለእኅቱም ለአልንጦንም ከእነርሱ ጋር ላሉ ቅዱሳን ሁሉ ሰላምታ አቅርቡልኝ።
16Sveiciniet viens otru ar svētu skūpstu! Jūs sveicina visas Kristus draudzes.
16በተቀደሰ አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ። የክርስቶስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
17Bet, brāļi, es jūs lūdzu, ņemiet vērā tos, kas rada šķelšanos un apgrēcību pret to mācību, ko jūs esat mācījušies, un izvairieties no viņiem!
17ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ የተማራችሁትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና ማሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንድትመለከቱ እለምናችኋለሁ፥ ከእነርሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ፤
18Jo tādi nekalpo Kristum, mūsu Kungam, bet savam vēderam. Ar saldajām runām un uzslavas vārdiem viņi pieviļ vientiesīgo sirdis.
18እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና፥ በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ።
19Bet jūsu paklausība ir izdaudzināta visās vietās. Tāpēc es priecājos par jums. Es tikai vēlos, lai jūs būtu sapratīgi labajā, bet vientiesīgi attiecībā pret ļaunu.
19መታዘዛችሁ ለሁሉ ተወርቶአልና፤ እንግዲህ በእናንተ ደስ ይለኛል፤ ነገር ግን ለበጎ ነገር ጥበበኞች ለክፉም የዋሆች እንድትሆኑ እወዳለሁ።
20Bet miera Dievs lai satriec sātanu visā drīzumā zem jūsu kājām! Mūsu Kunga Jēzus Kristus žēlastība lai ir ar jums!
20የሰላምም አምላክ ሰይጣንን ከእግራችሁ በታች ፈጥኖ ይቀጠቅጠዋል። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
21Jūs sveicina mans līdzstrādnieks Timotejs un mani tuvinieki: Lucijs un Jāsons, un Sosipatrs.
21አብሮኝ የሚሠራ ጢሞቴዎስ ዘመዶቼም ሉቂዮስና ኢያሶን ሱሲጴጥሮስም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
22Es, Tercijs, šīs vēstules rakstītājs, sveicinu jūs Kungā.
22ይህን መልእክት የጻፍሁ እኔ ጤርጥዮስ በጌታ ሰላምታ አቀርብላችኋለሁ።
23Jūs sveicina Gajs, mans viesis, un visa draudze. Jūs sveicina Erasts, pilsētas mantzinis, un brālis Kvarts.
23የእኔና የቤተ ክርስቲያን ሁሉ አስተናጋጅ ጋይዮስ ሰላምታ ያቀርብላችኋል። የከተማው መጋቢ ኤርስጦስ ወንድማችንም ቁአስጥሮስ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
24Mūsu Kunga Jēzus Kristus žēlastība lai ir ar jums visiem! Amen.
24የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን፤ አሜን።
25Bet Viņam, kas spējīgs jūs stiprināt sakaņā ar manu evaņģēliju un Jēzus Kristus vēstījumu, saskaņā ar noslēpumu atklāšanu, kas no mūžības bija noslēpts,
25እንግዲህ እንደ ወንጌሌ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስም እንደ ተሰበከ፥ ከዘላለም ዘመንም የተሰወረው አሁን ግን የታየው በነቢያትም መጻሕፍት የዘላለም እግዚአብሔር እንደ አዘዘ ለእምነት መታዘዝ ይሆን ዘንድ ለአሕዛብ ሁሉ የታወቀው ምሥጢር እንደ ተገለጠ መጠን ሊያበረታችሁ ለሚችለው፥
26(Kas tagad uz mūžīgā Dieva pavēli atklāts ar praviešu rakstiem, lai paklausītu ticībai), kas visām tautām pasludināts,
27ብቻውን ጥበብ ላለው ለእግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።
27Vienīgajam visugudrajam Dievam caur Jēzu Kristu lai ir gods un slava mūžīgi mūžos! Amen.