Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Peter

4

1Kadangi Kristus kentėjo kūnu už mus, tai ir jūs apsiginkluokite ta pačia mintimi,­nes kas kenčia kūnu, tas pametė nuodėmę,
1ክርስቶስም በሥጋ ስለ እኛ መከራን ስለተቀበለ፥ ከእንግዲህ ወዲህ በሥጋ ልትኖሩ በቀረላችሁ ዘመን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሰው ምኞት እንዳትኖሩ፥ እናንተ ደግሞ ያን አሳብ እንደ ዕቃ ጦር አድርጋችሁ ያዙት፥ በሥጋ መከራን የተቀበለ ኃጢአትን ትቶአልና።
2kad likusį laiką kūne gyventų nebe žmonių aistromis, o Dievo valia.
3የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።
3Gana, kad praėjusį laiką buvome pasidavę pagonių valiai ir gyvenome gašliai, geidulingai, girtuokliavome, ūžavome, puotavome ir pasiduodavome bjaurioms stabmeldystėms.
4በዚህም ነገር ወደዚያ መዳራት ብዛት ከእነርሱ ጋር ስለማትሮጡ እየተሳደቡ ይደነቃሉ፤
4Todėl jiems stebėtina, kad jūs nebebėgate kartu su jais pasinerti į tą patį ištvirkimo potvynį, ir jie piktžodžiauja.
5ግን እነርሱ በሕያዋንና በሙታን ላይ ሊፈርድ ለተዘጋጀው መልስ ይሰጣሉ።
5Jie turės duoti apyskaitą Tam, kuris pasiruošęs teisti gyvuosius ir mirusiuosius.
6እንደሰዎች በሥጋ እንዲፈረድባቸው በመንፈስ ግን እንደ እግዚአብሔር እንዲኖሩ ስለዚህ ምክንያት ወንጌል ለሙታን ደግሞ ተሰብኮላቸው ነበርና።
6Todėl buvo paskelbta Evangelija ir mirusiems, kad jie, nors ir nuteisti kūne kaip žmonės, gyventų dvasia kaip Dievas.
7ዳሩ ግን የነገር ሁሉ መጨረሻ ቀርቦአል። እንግዲህ እንደ ባለ አእምሮ አስቡ፥
7Visų dalykų galas arti. Todėl būkite blaivūs ir budėkite maldose.
8ትጸልዩም ዘንድ በመጠን ኑሩ፤ ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናልና ከሁሉ በፊት እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ።
8Visų pirma karštai mylėkite vienas kitą, nes meilė uždengia gausybę nuodėmių.
9ያለ ማንጐራጐር እርስ በርሳችሁ እንግድነትን ተቀባበሉ፤
9Būkite tarpusavyje svetingi be murmėjimo.
10ልዩ ልዩን የእግዚአብሔርን ጸጋ ደጋግ መጋቢዎች እንደ መሆናችሁ፥ እያንዳንዳችሁ የጸጋን ስጦታ እንደ ተቀበላችሁ መጠን በዚያው ጸጋ እርስ በርሳችሁ አገልግሉ፤
10Tarnaukite vieni kitiems kaip geri visokeriopos Dievo malonės tvarkytojai, sulig kiekvieno gautąja dovana.
11ማንም ሰው የሚናገር ቢሆን፥ እንደ እግዚአብሔር ቃል ይናገር፤ የሚያገለግልም ቢሆን፥ እግዚአብሔር በሚሰጠኝ ኃይል ነው ብሎ ያገልግል፤ ክብርና ሥልጣን እስከ ዘላለም ድረስ ለእርሱ በሚሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይከብር ዘንድ፤ አሜን።
11Jei kas kalba, tekalba kaip Dievo žodžius; jei kas tarnauja, tegul tarnauja pagal Dievo teikiamus sugebėjimus, kad visuose dalykuose per Jėzų Kristų būtų pašlovintas Dievas. Jam šlovė ir valdžia per amžių amžius! Amen.
12ወዳጆች ሆይ፥ በእናንተ መካከል እንደ እሳት ሊፈትናችሁ ስለሚሆነው መከራ ድንቅ ነገር እንደ መጣባችሁ አትደነቁ፤
12Mylimieji, nesistebėkite, kad jus degina ugnis, lyg jums būtų atsitikę kas keista, nes taip darosi jums išbandyti.
13ነገር ግን ክብሩ ሲገለጥ ደግሞ ሐሤት እያደረጋችሁ ደስ እንዲላችሁ፥ በክርስቶስ መከራ በምትካፈሉበት ልክ ደስ ይበላችሁ።
13Verčiau džiaukitės, dalyvaudami Kristaus kentėjimuose, kad ir tada, kai Jo šlovė apsireikš, galėtumėte džiūgauti dideliu džiaugsmu.
14ስለ ክርስቶስ ስም ብትነቀፉ የክብር መንፈስ የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ላይ ያርፋልና ብፁዓን ናችሁ።
14Jei jus užgaulioja dėl Jėzaus vardo,­jūs palaiminti, nes šlovės ir Dievo Dvasia ilsisi ant jūsų. Jų Ji keikiama, o jūsų­šlovinama.
15ከእናንተ ማንም ነፍሰ ገዳይ ወይም ሌባ ወይም ክፉ አድራጊ እንደሚሆን ወይም በሌሎች ጒዳይ እንደሚገባ ሆኖ መከራን አይቀበል፤
15Tik tegul niekas iš jūsų nekenčia kaip žmogžudys, vagis, piktadarys ar įkyruolis, besikišąs į kitų reikalus.
16ክርስቲያን እንደሚሆን ግን መከራን ቢቀበል ስለዚህ ስም እግዚአብሔርን ያመስግን እንጂ አይፈር።
16Bet jei kenčia kaip krikščionis, tegul nesigėdija, o tešlovina dėl to Dievą.
17ፍርድ ከእግዚአብሔር ቤት ተነሥቶ የሚጀመርበት ጊዜ ደርሶአልና፤ አስቀድሞም በእኛ የሚጀመር ከሆነ ለእግዚአብሔር ወንጌል የማይታዘዙ መጨረሻቸው ምን ይሆን?
17Nes jau metas prasidėti teismui nuo Dievo namų; ir jeigu jis pirmiausia prasideda nuo mūsų, tai koks galas laukia tų, kurie neklauso Dievo Evangelijos?!
18ጻድቅም በጭንቅ የሚድን ከሆነ ዓመፀኛውና ኃጢአተኛው ወዴት ይታይ ዘንድ አለው?
18Ir “jeigu teisusis vos ne vos išsigelbės, tai kur pasidės bedievis ir nusidėjėlis!”
19ስለዚህ ደግሞ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መከራን የሚቀበሉ፥ መልካምን እያደረጉ ነፍሳቸውን ለታመነ ፈጣሪ አደራ ይስጡ።
19Todėl tie, kurie kenčia pagal Dievo valią, tepaveda savo sielas Jam, ištikimajam Kūrėjui, darydami gera.