Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Peter

5

1Jūsų vyresniuosius raginu aš, irgi vyresnysis, Kristaus kentėjimų liudytojas ir dalyvis šlovės, kuri bus apreikšta:
1እንግዲህ እኔ፥ ከእነርሱ ጋር ሽማግሌ የክርስቶስም መከራ ምስክር ደግሞም ሊገለጥ ካለው ክብር ተካፋይ የሆንሁ፥ በመካከላቸው ያሉትን ሽማግሌዎች እመክራቸዋለሁ፤
2ganykite pas jus esančią Dievo kaimenę, prižiūrėdami ją ne iš prievartos, bet noriai, ne dėl nešvaraus pelno, bet uoliai,
2በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ ሳይሆን፥ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ረብ በመመኘት ሳይሆን ጐብኙት፤
3ne kaip viešpataujantys jums patikėtiems, bet būdami pavyzdžiu kaimenei.
3ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማኅበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ፤
4O kai pasirodys Vyriausiasis Ganytojas, jūs gausite nevystantį šlovės vainiką.
4የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ።
5Taip pat jūs, jaunesnieji, būkite klusnūs vyresniesiems. Ir visi, paklusdami vieni kitiems, apsivilkite nuolankumu, nes “Dievas išdidiems priešinasi, o nuolankiesiems teikia malonę”.
5እንዲሁም፥ ጐበዞች ሆይ፥ ለሽማግሌዎች ተገዙ፤ ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ፥ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል።
6Tad nusižeminkite po galinga Dievo ranka, kad Jis išaukštintų jus metui atėjus.
6እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤
7Meskite ant Jo savo rūpesčius, nes Jis jumis rūpinasi.
7እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።
8Būkite blaivūs ir budrūs, nes jūsų priešas velnias slankioja aplinkui kaip riaumojantis liūtas, tykodamas kurį nors praryti.
8በመጠን ኑሩ ንቁም፥ ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና፤
9Pasipriešinkite jam tvirtu tikėjimu, žinodami, kad tokius pačius kentėjimus patiria jūsų broliai pasaulyje.
9በዓለም ያሉት ወንድሞቻችሁ ያን መከራ በሙሉ እንዲቀበሉ እያወቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት።
10O visokeriopos malonės Dievas, pašaukęs mus į savo amžinąją šlovę Kristuje Jėzuje, pats jus, trumpai pakentėjusius, ištobulins, sutvirtins, sustiprins ir pastatys ant tvirto pagrindo.
10በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዘላለም ክብሩ የጠራችሁ የጸጋ ሁሉ አምላክ ለጥቂት ጊዜ መከራን ከተቀበላችሁ በኋላ ራሱ ፍጹማን ያደርጋችኋል ያጸናችሁምል ያበረታችሁማል።
11Jam šlovė ir valdžia per amžių amžius! Amen.
11ለእርሱ ክብርና ኃይል እስከዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን።
12Per Silvaną, ištikimąjį brolį,­tokiu jį laikau,­aš jums trumpai parašiau, ragindamas ir liudydamas, kad tai yra tikroji Dievo malonė, kurioje jūs stovite.
12እየመከርኋችሁና የምትቆሙባት ጸጋ እውነትኛ የእግዚአብሔር ጸጋ እንድትሆን እየመሰከርሁላችሁ፥ የታመነ ወንድም እንደ ሆነ በቈጠርሁት በስልዋኖስ እጅ በአጭሩ ጽፌላችኋለሁ።
13Jus sveikina kartu išrinktoji Babilone ir mano sūnus Morkus.
13ከእናንተ ጋር ተመርጣ በባቢሎን ያለች ቤተ ክርስቲያን ልጄም ማርቆስ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
14Sveikinkite vieni kitus meilės pabučiavimu! Ramybė jums visiems, kurie esate Kristuje Jėzuje! Amen.
14በፍቅር አሳሳም እርስ በርሳችሁ ሰላምታ ተሰጣጡ። በክርስቶስ ላላችሁ ለሁላችሁ ሰላም ይሁን። አሜን።