1Jūs patys, broliai, žinote, kad mūsų apsilankymas pas jus nebuvo veltui.
1ወንድሞች ሆይ፥ ራሳችሁ ወደ እናንተ መግባታችን ከንቱ እንዳልሆነ ታውቃላችሁና።
2Prieš tai, kaip patys žinote, nukentėję ir paniekinti Filipuose, buvome drąsūs Dieve ir skelbėme jums Evangeliją esant dideliam pasipriešinimui.
2ነገር ግን እንደምታውቁት በፊልጵስዩስ አስቀድመን መከራ ተቀብለን ተንገላትተንም፥ በብዙ ገድል የእግዚአብሔርን ወንጌል ለእናንተ እንናገር ዘንድ በአምላካችን ደፈርን።
3Juk mūsų skelbimas plaukia ne iš klaidos, nei iš netyro nusistatymo, nei iš klastingumo.
3ልመናችን ከስሕተት ወይም ከርኵሰት ወይም ከተንኰል አልነበረምና፤
4Dievo pripažinti tinkami, kad mums būtų patikėta Evangelija, ją ir skelbiame taip, kad patiktume ne žmonėms, bet Dievui, kuris tiria mūsų širdis.
4ነገር ግን ወንጌልን አደራ ይሰጠን ዘንድ እግዚአብሔር የታመንን ሆነን እንዳገኘን መጠን፥ እንዲሁ እንናገራለን፥ ልባችንን የሚመረምር እግዚአብሔርን እንጂ ሰውን ደስ እንደምናሰኝ አይደለም።
5Kaip žinote, niekada nepasižymėjome pataikaujančiomis kalbomis ir paslėptu godumu,Dievas yra liudytojas,
5እንደምታውቁ፥ እያቈላመጥን ከቶ አልተናገርንም፥ እግዚአብሔርም እንደሚመሰክር እያመካኘን በመጐምጀት አልሠራንም፤
6niekada neieškojome žmonių garbės, nei tarp jūsų, nei kitur. Būdami Kristaus apaštalai, galėjome būti jums našta,
6የክርስቶስም ሐዋርያት እንደ መሆናችን ልንከብድባችሁ ስንችል፥ ከእናንተ ቢሆን ወይም ከሌሎች ክብርን ከሰው አልፈለግንም።
7vis dėlto pas jus buvome švelnūs, tarsi maitinanti motina, globojanti savo kūdikius.
7ነገር ግን ሞግዚት የራስዋን ልጆች እንደምትከባከብ፥ በመካከላችሁ የዋሆች ሆንን፤
8Taip jus mylėdami, troškome pasidalyti su jumis ne tik Dievo Evangelija, bet ir savo gyvybe, nes tapote mums brangūs.
8እንዲሁም እያፈቀርናችሁ የእግዚአብሔርን ወንጌል ለማካፈል ብቻ ሳይሆን የገዛ ነፍሳችንን ደግሞ እናካፍላችሁ ዘንድ በጎ ፈቃዳችን ነበረ፥ ለእኛ የተወደዳችሁ ሆናችሁ ነበርና።
9Jūs, broliai, atsimenate mūsų triūsą ir pastangas: dirbdami per dienas ir naktis, kad neapsunkintume nė vieno iš jūsų, skelbėme jums Dievo Evangeliją.
9ወንድሞች ሆይ፥ ድካማችንና ጥረታችን ትዝ ይላችኋልና፤ ከእናንተ በአንዱ ስንኳ እንዳንከብድበት ሌሊትና ቀን እየሠራን፥ የእግዚአብሔርን ወንጌል ለእናንተ ሰበክን።
10Ir jūs, ir Dievas gali paliudyti, kaip šventai, teisingai ir nepriekaištingai elgėmės su jumis, įtikėjusiais.
10በእናንተ በምታምኑ ዘንድ በእንዴት ያለ ቅድስናና ጽድቅ ነቀፋም በሌለበት ኑሮ እንደ ሄድን፥ እናንተና እግዚአብሔር ምስክሮች ናችሁ፤
11Jūs žinote, kaip kiekvieną iš jūsų raginome, kalbinome, maldavome, tarsi tėvas savo vaikus,
11ወደ መንግሥቱ ወደ ክብሩም ለጠራችሁ ለእግዚአብሔር እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እየመከርንና እያጸናን እየመሰከርንላችሁም፥ አባት ለልጆቹ እንደሚሆን ለእያንዳንዳችሁ እንደ ሆንን ታውቃላችሁና።
12kad elgtumėtės kaip dera prieš Dievą, kuris jus šaukia į savo karalystę ir šlovę.
13ስለዚህም የመልእክትን ቃል እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ከእኛ በተቀበላችሁ ጊዜ፥ በእውነት እንዳለ በእናንተ በምታምኑ ደግሞ እንደሚሠራ እንደ እግዚአብሔር ቃል እንጂ እንደ ሰው ቃል አድርጋችሁ ስላልተቀበላችሁት፥ እኛ ደግሞ እግዚአብሔርን ሳናቋርጥ እናመሰግናለን።
13Todėl ir mes be paliovos dėkojame Dievui, kad, priėmę Dievo žodį, kurį girdėjote iš mūsų, priėmėte jį ne kaip žmonių žodį, bet, kas jis iš tikro yra,kaip Dievo žodį, kuris ir veikia jumyse, tikinčiuosiuose.
14እናንተ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በይሁዳ የሚኖሩትን በክርስቶስ ኢየሱስ ያሉትን የእግዚአብሔርን ማኅበሮች የምትመስሉ ሆናችኋልና፤ እነርሱ ከአይሁድ መከራ እንደ ተቀበሉ፥ እናንተ ደግሞ ያንን መከራ ከአገራችሁ ሰዎች ተቀብላችኋልና።
14Jūs, broliai, tapote sekėjais Dievo bažnyčių Kristuje Jėzuje, kurios yra Judėjoje. Jūs tą patį iškentėjote nuo savo tautiečių, kaip ir jos nuo žydų,
15እነዚያም ጌታን ኢየሱስን ደግሞ ገደሉ ነቢያትንም እኛንም አሳደዱ፥ እግዚአብሔርንም ደስ አያሰኙም፥ ሰዎችንም ሁሉ ይቃወማሉ፥
15kurie nužudė Viešpatį Jėzų ir savo pranašus ir persekiojo mus. Jie nepatinka Dievui ir yra priešiški visiems žmonėms,
16ሁልጊዜ ኃጢአታቸውን ይፈጽሙ ዘንድ አሕዛብ እንዲድኑ እንዳንናገራቸው ይከለክሉናልና። ነገር ግን ቍጣው ወደ እነርሱ ፈጽሞ ደርሶአል።
16nes draudžia mums skelbti Evangeliją pagonims, kad šie būtų išgelbėti. Taip jie nuolat pildo savo nuodėmių saiką, ir jiems artinasi galutinė Dievo rūstybė.
17እኛ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ በልብ ያይደለ ፊት ለፊት ለጥቂት ጊዜ አጥተናችሁ፥ በብዙ ናፍቆት ፊታችሁን ለማየት እጅግ ሞከርን፤
17O mes, broliai, kuriam laikui atskirti nuo jūsų,žinoma, tik kūnu, ne širdimi,be galo pasiilgę, labai troškome išvysti jūsų veidus.
18ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን።
18Todėl ruošėmės atvykti pas jus,bent jau aš, Paulius, ruošiausi kartą ir kitą,tačiau mums sutrukdė šėtonas.
19ተስፋችን ወይስ ደስታችን ወይስ የትምክህታችን አክሊል ማን ነው? በጌታችን በኢየሱስ ፊት በመምጣቱ እናንተ አይደላችሁምን?
19Kas gi yra mūsų viltis, džiaugsmas ir pasigyrimo vainikas? Argi ne jūs prieš mūsų Viešpatį Jėzų Kristų Jo atėjimo metu?
20እናንተ ክብራችን ደስታችንም ናችሁና።
20Taip, jūs esate mūsų šlovė ir džiaugsmas!