1O vienas vyras, vardu Ananijas, su savo žmona Sapfyra pardavė nuosavybę
1ሐናንያም የተባለ አንድ ሰው ሰጲራ ከተባለች ከሚስቱ ጋር መሬት ሸጠ፥
2ir, žmonai pritariant, pasiliko dalį gautų pinigų, o kitą dalį atnešė ir padėjo prie apaštalų kojų.
2ሚስቱም ደግሞ ስታውቅ ከሽያጩ አስቀረና እኩሌታውን አምጥቶ በሐዋርያት እግር አጠገብ አኖረው።
3Petras paklausė: “Ananijau, kodėl šėtonas užvaldė tavo širdį, kad tu pamelavai Šventajai Dvasiai, pasilikdamas dalį už žemę gautų pinigų?
3ጴጥሮስም። ሐናንያ ሆይ፥ መንፈስ ቅዱስን ታታልልና ከመሬቱ ሽያጭ ታስቀር ዘንድ ሰይጣን በልብህ ስለ ምን ሞላ?
4Argi nebuvo tavo tai, ką turėjai, ir ką gavai pardavęs, argi nebuvo tavo žinioje? Tai kodėl gi taip sumanei savo širdyje? Tu pamelavai ne žmonėms, bet Dievui!”
4ሳትሸጠው የአንተ አልነበረምን? ከሸጥኸውስ በኋላ በሥልጣንህ አልነበረምን? ይህን ነገር ስለ ምን በልብህ አሰብህ? እግዚአብሔርን እንጂ ሰውን አልዋሸህም አለው።
5Išgirdęs tuos žodžius, Ananijas krito ant žemės ir mirė. Didelė baimė apėmė visus tai girdėjusius.
5ሐናንያም ይህን ቃል ሰምቶ ወደቀ ሞተም፤ በሰሙትም ሁሉ ላይ ታላቅ ፍርሃት ሆነ።
6Keli jaunuoliai pakilo, suvyniojo jį marškomis, išnešė ir palaidojo.
6ጐበዞችም ተነሥተው ከፈኑት አውጥተውም ቀበሩት።
7Po kokių trijų valandų atėjo jo žmona, kuri nežinojo, kas buvo atsitikę.
7ከሦስት ሰዓት ያህል በኋላም ሚስቱ የሆነውን ሳታውቅ ገባች።
8Petras ją paklausė: “Pasakyk man, ar už tiek pardavėte sklypą?” “Taip, už tiek”,atsakė ji.
8ጴጥሮስም መልሶ። እስቲ ንገሪኝ፥ መሬታችሁን ይህን ለሚያህል ሸጣችሁትን? አላት። እርስዋም። አዎን፥ ይህን ለሚያህል ነው አለች።
9Tada Petras jai tarė: “Kodėl susitarėte mėginti Viešpaties Dvasią? Štai ties durimis skamba žingsniai tų, kurie palaidojo tavo vyrą. Jie ir tave išneš”.
9ጴጥሮስም። የጌታን መንፈስ ትፈታተኑ ዘንድ ስለ ምን ተስማማችሁ? እነሆ፥ ባልሽን የቀበሩት ሰዎች እግር በደጅ ነው አንቺንም ያወጡሻል አላት።
10Bematant ji susmuko jam po kojų ir mirė. Atėję jaunuoliai rado ją negyvą, nunešė ir palaidojo šalia vyro.
10ያን ጊዜም በእግሩ አጠገብ ወደቀች ሞተችም፤ ጐበዞችም ሲገቡ ሞታ አገኙአት አውጥተውም በባልዋ አጠገብ ቀበሩአት።
11Didelė baimė apėmė visą bažnyčią ir visus, kurie apie tai išgirdo.
11በቤተ ክርስቲያን ሁሉና ይህንም በሰሙ ሁሉ ላይ ታላቅ ፍርሃት ሆነ።
12Per apaštalų rankas žmonėse vyko daug ženklų ir stebuklų. Visi jie vieningai rinkdavosi Saliamono stoginėje.
12በሐዋርያትም እጅ ብዙ ምልክትና ድንቅ በሕዝብ መካከል ይደረግ ነበር፤ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው በሰሎሞን ደጅ መመላለሻ ነበሩ።
13Iš kitų nė vienas neišdrįsdavo prie jų prisidėti. Žmonės juos labai gerbė.
13ከሌሎችም አንድ ስንኳ ሊተባበራቸው የሚደፍር አልነበረም፥
14Ir vis labiau augo būrys vyrų ir moterų, įtikėjusių Viešpatį.
14ሕዝቡ ግን ያከብሩአቸው ነበር፤ የሚያምኑትም ከፊት ይልቅ ለጌታ ይጨመሩለት ነበር፤ ወንዶችና ሴቶችም ብዙ ነበሩ።
15Net į gatves nešdavo ligonius ir guldydavo ant neštuvų bei lovų, kad, Petrui praeinant pro šalį, bent jo šešėlis kristų ant gulinčiųjų.
15ስለዚህም ጴጥሮስ ሲያልፍ ጥላውም ቢሆን ከእነርሱ አንዱን ይጋርድ ዘንድ ድውያንን ወደ አደባባይ አውጥተው በአልጋና በወሰካ ያኖሩአቸው ነበር።
16Taip pat ir iš aplinkinių miestų daugybė žmonių keliaudavo į Jeruzalę, gabendami sergančius ir netyrųjų dvasių kankinamus, ir visi jie būdavo pagydomi.
16ደግሞም በኢየሩሳሌም ዙሪያ ካለችው ከተማ ድውያንንና በርኵሳን መናፍስት የተሣቀዩትን እያመጡ ብዙ ሰዎች ይሰበስቡ ነበር፤ ሁሉም ይፈወሱ ነበር።
17Tuomet sujudo vyriausiasis kunigas ir visi jo šalininkai iš sadukiejų partijos. Degdami pavydu,
17ሊቀ ካህናቱ ግን የሰዱቃውያን ወገን ሆነውም ከእርሱ ጋር የነበሩት ሁሉ ተነሡ ቅንዓትም ሞላባቸው።
18jie suėmė apaštalus ir įmetė juos į viešą kalėjimą.
18በሐዋርያትም ላይ እጃቸውን ጭነው በሕዝቡ ወኅኒ ውስጥ አኖሩአቸው።
19Bet Viešpaties angelas naktį atidarė kalėjimo vartus, išvedė juos ir tarė:
19የጌታ መልአክ ግን በሌሊት የወኅኒውን ደጅ ከፍቶ አወጣቸውና።
20“Eikite ir, atsistoję šventykloje, skelbkite žmonėms visus šio Gyvenimo žodžius”.
20ሂዱና ቆማችሁ የዚህን ሕይወት ቃል ሁሉ ለሕዝብ በመቅደስ ንገሩ አላቸው።
21Tai išgirdę, jie auštant nuėjo į šventyklą ir ėmė mokyti. Tuo metu vyriausiasis kunigas ir jo šalininkai sukvietė sinedrioną bei visą Izraelio tautos vyresniųjų tarybą ir nusiuntė į kalėjimą tarnus atvesti apaštalų.
21በሰሙም ጊዜ ማልደው ወደ መቅደስ ገብተው አስተማሩ። ግን ሊቀ ካህናቱና ከእርሱ ጋር የነበሩት መጥተው ሸንጎውንና የእስራኤልን ልጆች ሽማግሌዎች ሁሉ በአንድነት ጠሩ፥ ያመጡአቸውም ዘንድ ወደ ወኅኒ ላኩ።
22Bet tarnai nuėję nerado jų kalėjime ir sugrįžę pranešė:
22ሎሌዎችም መጥተው በወኅኒው አላገኙአቸውም፤ ተመልሰውም። ወኅኒው በጣም በጥንቃቄ ተዘግቶ ጠባቂዎችም በደጁ ፊት ቆመው አገኘን፥ በከፈትን ጊዜ ግን በውስጡ አንድ ስንኳ አላገኘንም አሉአቸው።
23“Kalėjimą radome saugiai užrakintą ir sargybinius stovinčius prie vartų. Bet atidarę nieko viduje neradome!”
24የመቅደስ አዛዥና የካህናት አለቆችም ይህን ነገር በሰሙ ጊዜ። እንጃ ይህ ምን ይሆን? እያሉ ስለ እነርሱ አመነቱ።
24Išgirdę tokį pranešimą, vyriausiasis kunigas, šventyklos apsaugos viršininkas ir aukštieji kunigai suglumo, nesuprasdami, ką tai galėtų reikšti.
25አንድ ሰውም መጥቶ። እነሆ፥ በወኅኒ ያኖራችኋቸው ሰዎች እየቆሙ ሕዝቡንም እያስተማሩ በመቅደስ ናቸው ብሎ አወራላቸው።
25Tuomet kažkas atėjęs pranešė: “Tie vyrai, kuriuos buvote uždarę kalėjime, stovi šventykloje ir moko žmones”.
26በዚያን ጊዜ አዛዡ ከሎሌዎች ጋር ሄዶ አመጣቸው፥ በኃይል ግን አይደለም፤ ሕዝቡ እንዳይወግሩአቸው ይፈሩ ነበርና።
26Tada viršininkas su tarnais nuėjo ir atsivedė juos be prievartos, nes bijojo žmonių, kad neužmėtytų akmenimis.
27አምጥተውም በሸንጎ አቆሙአቸው።
27Taigi atsivedę apaštalus, pastatė juos sinedrione. Vyriausiasis kunigas jiems tarė:
28ሊቀ ካህናቱም። በዚህ ስም እንዳታስተምሩ አጥብቀን አላዘዝናችሁምን? እነሆም፥ ኢየሩሳሌምን በትምህርታችሁ ሞልታችኋል፤ የዚያንም ሰው ደም በእኛ ታመጡብን ዘንድ ታስባላችሁ ብሎ ጠየቃቸው።
28“Argi mes jums drauste neuždraudėme mokyti tuo vardu, o štai jūs užtvindėte Jeruzalę savo mokymu ir dar norite ant mūsų užtraukti to žmogaus kraują”.
29ጴጥሮስና ሐዋርያትም መልሰው አሉ። ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል።
29Petras ir apaštalai atsakė: “Dievo reikia klausyti labiau negu žmonių.
30እናንተ በእንጨት ላይ ሰቅላችሁ የገደላችሁትን ኢየሱስን የአባቶቻችን አምላክ አስነሣው፤
30Mūsų tėvų Dievas prikėlė Jėzų, kurį jūs nužudėte, pakabindami ant medžio.
31ይህን እግዚአብሔር፥ ለእስራኤል ንስሐን የኃጢአትንም ስርየት ይሰጥ ዘንድ፥ ራስም መድኃኒትም አድርጎ በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው።
31Dievas išaukštino Jį savo dešine kaip Karalių ir Išgelbėtoją, kad suteiktų Izraeliui atgailą ir nuodėmių atleidimą.
32እኛም ለዚህ ነገር ምስክሮች ነን፥ ደግሞም እግዚአብሔር ለሚታዘዙት የሰጠው መንፈስ ቅዱስ ምስክር ነው።
32Mes esame Jo ir tų įvykių liudytojai, taip pat ir Šventoji Dvasia, kurią Dievas suteikė tiems, kurie Jam paklūsta”.
33እነርሱም ሲሰሙ በጣም ተቈጡ ሊገድሉአቸውም አሰቡ።
33Girdėdami šituos žodžius, jie baisiai įtūžo ir ketino juos užmušti.
34ነገር ግን በሕዝብ ሁሉ ዘንድ የከበረ የሕግ መምህር ገማልያል የሚሉት አንድ ፈሪሳዊ በሸንጎ ተነሥቶ ሐዋርያትን ጥቂት ፈቀቅ እንዲያደርጉአቸው አዘዘ፥
34Tuomet sinedrione pakilo vienas fariziejus, vardu Gamalielis, visos tautos gerbiamas Įstatymo mokytojas. Jis įsakė trumpam išvesti apaštalus
35እንዲህም አላቸው። የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ስለ እነዚህ ሰዎች ምን እንደምታደርጉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።
35ir tarė susirinkusiems: “Vyrai izraelitai! Gerai pagalvokite, kaip pasielgti su šitais žmonėmis.
36ከዚህ ወራት አስቀድሞ ቴዎዳስ። እኔ ታላቅ ነኝ ብሎ ተነሥቶ ነበርና፥ አራት መቶ የሚያህሉ ሰዎችም ከእርሱ ጋር ተባበሩ፤ እርሱም ጠፋ የሰሙትም ሁሉ ተበተኑ እንደ ምናምንም ሆኑ።
36Juk prieš kiek laiko buvo iškilęs Teudas, kuris laikė save kažkuo nepaprastu. Prie jo prisidėjo apie keturis šimtus vyrų, bet jis buvo užmuštas, visi šalininkai išsisklaidė ir nuėjo niekais.
37ከዚህ በኋላ ሰዎች በተጻፉበት ዘመን የገሊላው ይሁዳ ተነሣ ብዙ ሰዎችንም አሸፍቶ አስከተለ፤ እርሱም ጠፋ የሰሙትም ሁሉ ተበታተኑ።
37Po jo, gyventojų surašymo dienomis, atsirado Judas Galilėjietis ir patraukė nemažai žmonių paskui save. Jis taip pat žuvo, o visi jo sekėjai buvo išblaškyti.
38አሁንም እላችኋለሁ። ከእነዚህ ሰዎች ተለዩ ተዉአቸውም፤ ይህ አሳብ ወይም ይህ ሥራ ከሰው እንደ ሆነ ይጠፋልና፤
38Todėl dabar jums sakau: palikite šituos žmones ramybėje ir paleiskite juos. Jei šis sumanymas ir ši veikla iš žmonių,jie žlugs savaime,
39ከእግዚአብሔር እንደ ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም፥ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ።
39o jeigu tai iš Dievo, tai jūs nepajėgsite jų sunaikinti. Žiūrėkite, kad nepasirodytumėte kovojantys prieš Dievą!” Jie paklausė jo patarimo.
40ሰሙትም፥ ሐዋርያትንም ወደ እነርሱ ጠርተው ገረፉአቸው፥ በኢየሱስም ስም እንዳይናገሩ አዝዘው ፈቱአቸው።
40Pasišaukę apaštalus, nuplakdino juos, uždraudė kalbėti Jėzaus vardu ir paleido.
41እነርሱም ስለ ስሙ ይናቁ ዘንድ የተገባቸው ሆነው ስለ ተቈጠሩ ከሸንጎው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ፤
41O tie ėjo iš sinedriono džiaugdamiesi, kad buvo palaikyti vertais dėl Jėzaus vardo iškęsti paniekinimą.
42ዕለት ዕለትም በመቅደስና በቤታቸው ስለ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ማስተማርንና መስበክን አይተዉም ነበር።
42Kiekvieną dieną šventykloje ir po namus jie nesiliovė mokyti bei skelbti Jėzų Kristumi.