Lithuanian

Amharic: New Testament

Acts

6

1Tomis dienomis, mokinių skaičiui augant, tarp graikiškai kalbančiųjų kilo nepasitenkinimas vietiniais žydais, nes kasdieniniame aprūpinime būdavo aplenkiamos jų našlės.
1በዚህም ወራት ደቀ መዛሙርት እየበዙ ሲሄዱ ከግሪክ አገር መጥተው የነበሩት አይሁድ በይሁዳ ኖረው በነበሩት አይሁድ አንጐራጐሩባቸው፥ በየቀኑ በተሠራው አገልግሎት መበለቶቻቸውን ችላ ይሉባቸው ነበርና።
2Tuomet dvylika sušaukė mokinių susirinkimą ir tarė: “Nedera mums palikus Dievo žodį tarnauti prie stalų.
2አሥራ ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ሁሉን ጠርተው እንዲህ አሉአቸው። የእግዚአብሔር ቃል ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም።
3Todėl, broliai, išsirinkite iš savųjų septynis vyrus, turinčius gerą vardą, kupinus Šventosios Dvasios ir išminties. Mes juos paskirsime tam darbui,
3ወንድሞች ሆይ፥ በመልካም የተመሰከረላቸውን መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፥ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፤
4o patys toliau atsidėsime maldai ir žodžio tarnavimui”.
4እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን።
5Šis pasiūlymas patiko visam susirinkimui, ir jie išsirinko Steponą, vyrą pilną tikėjimo ir Šventosios Dvasios, Pilypą, Prochorą, Nikanorą, Timoną, Parmeną ir Mikalojų, prozelitą iš Antiochijos.
5ይህም ቃል ሕዝብን ሁሉ ደስ አሰኛቸው፤ እምነትና መንፈስ ቅዱስም የሞላበትን ሰው እስጢፋኖስን ፊልጶስንም ጵሮኮሮስንም ኒቃሮናንም ጢሞናንም ጳርሜናንም ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን የአንጾኪያውን ኒቆላዎስንም መረጡ።
6Juos pastatė prieš apaštalus, o šie melsdamiesi uždėjo ant jų rankas.
6በሐዋርያትም ፊት አቆሙአቸው፥ ከጸለዩም በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው።
7Dievo žodis klestėjo, ir mokinių skaičius Jeruzalėje smarkiai augo. Ir didelis kunigų būrys pakluso tikėjimui.
7የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፥ በኢየሩሳሌምም የደቀ መዛሙርት ቍጥር እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙ ሰዎች ለሃይማኖት የታዘዙ ሆኑ።
8Steponas, pilnas tikėjimo ir jėgos, darė žmonėse didžių stebuklų ir ženklų.
8እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር።
9Tuomet pakilo kai kurie iš vadinamosios libertinų sinagogos, iš kirėniečių, aleksandriečių ir iš Kilikijos bei Azijos ir ėmė ginčytis su Steponu.
9የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤
10Tačiau jie negalėjo atsispirti išminčiai ir Dvasiai, kurios įkvėptas jis kalbėjo.
10ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም።
11Tada jie papirko keletą vyrų, kad tie sakytų: “Mes girdėjome jį piktžodžiaujant Mozei ir Dievui”.
11በዚያን ጊዜ። በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ።
12Taip jie sukurstė minią, vyresniuosius bei Rašto žinovus, užpuolę sučiupo jį ir nusivedė į sinedrioną.
12ሕዝቡንና ሽማግሌዎችንም ጻፎችንም አናደዱ፥ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና።
13Ten pastatė melagingus liudytojus, kurie tvirtino: “Šitas žmogus nesiliauja kalbėjęs prieš šventąją vietą ir Įstatymą.
13ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤
14Mes girdėjome jį sakant, kad Jėzus iš Nazareto išgriaus šią vietą ir pakeis Mozės perduotus mums papročius”.
14ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ።
15Visi sėdintys sinedrione įsmeigė į jį akis ir matė jo veidą tarytum angelo veidą.
15በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት።