Lithuanian

Amharic: New Testament

Ephesians

1

1Paulius, Dievo valia Jėzaus Kristaus apaštalas, šventiesiems, gyvenantiems Efeze, ir ištikimiesiems Kristuje Jėzuje.
1በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ፥ በኤፌሶን ላሉት ቅዱሳን በክርስቶስ ኢየሱስም ላሉት ምእመናን፤
2Malonė jums ir ramybė nuo Dievo, mūsų Tėvo, ir Viešpaties Jėzaus Kristaus!
2ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
3Tebūna palaimintas Dievas, mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus Tėvas, kuris palaimino mus Kristuje visais dvasiniais palaiminimais danguje,
3በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።
4mus išrinkdamas Jame prieš pasaulio sutvėrimą, kad būtume šventi ir nekalti meile Jo akivaizdoje.
4ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።
5Geros valios nutarimu Jis iš anksto paskyrė mus įsūnyti per Jėzų Kristų
5በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን።
6Jo malonės šlovės gyriui, kuria padarė mus priimtinus Mylimajame.
6በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ።
7Jame turime atpirkimą per Jo kraują ir nuodėmių atleidimą pagal turtus Jo malonės,
7በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።
8kurią Jis dosniai suteikė mums su visa išmintimi ir supratimu,
8ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን።
9paskelbdamas mums savo valios paslaptį pagal savo palankumą, kaip nusprendė savyje,
9በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤
10kad, laikų pilnatvei atėjus, galėtų suvienyti Kristuje visa, kas yra tiek danguje, tiek ir žemėje.
10በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።
11Jame ir gavome palikimą, iš anksto paskirtą sutvarkymu To, kuris visa veikia pagal savo valios nutarimą,
11እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ፥ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን።
12kad pasitarnautume Jo šlovės gyriui mes, kurie nuo seno turėjome viltį Kristuje.
12ይኸውም፥ በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን እኛ ለክብሩ ምስጋና እንሆን ዘንድ ነው።
13Jame ir jūs, išgirdę tiesos žodį­ jūsų išgelbėjimo Evangeliją­ir įtikėję Juo, esate užantspauduoti pažadėtąja Šventąja Dvasia,
13እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤
14kuri yra mūsų paveldėjimo užstatas iki nuosavybės atpirkimo Jo šlovės gyriui.
14እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ፥ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል።
15Todėl ir aš, išgirdęs apie jūsų tikėjimą Viešpačiu Jėzumi ir apie jūsų meilę visiems šventiesiems,
15ስለዚህ እኔ ደግሞ በእናንተ ዘንድ ስለሚሆን በጌታ በኢየሱስ ስለ ማመንና ለቅዱሳን ሁሉ ስለሚሆን መውደድ ሰምቼ፥
16nesiliauju dėkojęs už jus, prisimindamas jus savo maldose,
16ስለ እናንተ እያመሰገንሁ ስጸልይ ስለ እናንተ ማሳሰብን አልተውም፤
17kad mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus Dievas, šlovės Tėvas, duotų jums išminties ir apreiškimo dvasią Jo pažinimui
17የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።
18ir apšviestų jūsų širdies akis, kad pažintumėte, kokia yra Jo pašaukimo viltis, kokie Jo palikimo šlovės turtai šventuosiuose
18ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
19ir kokia beribė Jo jėgos didybė mums, kurie tikime, veikiant jo galingai jėgai.
20ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም ከኃይልም ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው በክርስቶስ ባደረገው ሥራ የብርታቱ ጉልበት ይታያል፤
20Ja Jis veikė Kristuje, prikeldamas Jį iš numirusių ir pasodindamas savo dešinėje danguose,
22ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው።
21aukščiau už kiekvieną kunigaikštystę, valdžią, jėgą, viešpatystę ir už kiekvieną vardą, tariamą ne tik šiame amžiuje, bet ir būsimajame,
23እርስዋም አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት።
22ir visa paklojo po Jo kojomis, o Jį patį pastatė viršum visko, kad būtų galva bažnyčios,
23kuri yra Jo kūnas, pilnatvė To, kuris visa visame pripildo.