1Broliai, jei žmogus įpuola į kokią nuodėmę, jūs, dvasiniai žmonės, pataisykite tokį romumo dvasioje, žiūrėdami savęs, kad ir patys nebūtumėt sugundyti.
1ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት፤ አንተ ደግሞ እንዳትፈተን ራስህን ጠብቅ።
2Nešiokite vieni kitų naštas, ir taip įvykdysite Kristaus įstatymą.
2ከእናንተ እያንዳንዱ የአንዱን ሸክም ይሸከም እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ።
3O kas, būdamas niekas, tariasi esąs kažin kas, tas save apgaudinėja.
3አንዱ ምንም ሳይሆን ምንም የሆነ ቢመስለው ራሱን ያታልላልና።
4Tegul kiekvienas ištiria savo darbą, ir tada galės girtis pats sau, o ne kitam,
4ነገር ግን እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሥራ ይፈትን፥ ከዚያም በኋላ ስለ ሌላው ሰው ያልሆነ ስለ ራሱ ብቻ የሚመካበትን ያገኛል፤
5nes kiekvienas neš savo naštą.
5እያንዳንዱ የገዛ ራሱን ሸክም ሊሸከም ነውና።
6Kas mokomas žodžio, tegul dalijasi visais gerais dalykais su mokytoju.
6ነገር ግን ቃሉን የሚማር ከሚያስተምረው ጋር መልካምን ነገር ሁሉ ይከፋፈል።
7Neapsigaukite! Iš Dievo nepasišaipysi. Ką žmogus sėja, tą ir pjaus.
7አትሳቱ፤ እግዚአብሔር አይዘበትበትም። ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤
8Kas sėja savo kūnui, tas iš kūno pjaus supuvimą, o kas sėja Dvasiai, tas iš Dvasios pjaus amžinąjį gyvenimą.
8በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል።
9Nepavarkime daryti gera, nes savo metu pjausime derlių, jei nepailsime!
9ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።
10Tad, kol turime laiko, darykime gera visiems, o ypač tikėjimo namiškiams.
10እንግዲያስ ጊዜ ካገኘን ዘንድ ለሰው ሁሉ ይልቁንም ለሃይማኖት ቤተ ሰዎች መልካም እናድርግ።
11Žiūrėkite, kokiomis didelėmis raidėmis jums parašiau savo ranka.
11እንዴት ባሉ ታላላቆች ፊደላት በእጄ እንደ ጻፍሁላችሁ እዩ።
12Visi, kurie nori pasirodyti geri kūnu, verčia jus apsipjaustyti, kad tik jiems netektų kęsti persekiojimų dėl Kristaus kryžiaus.
12በሥጋ መልካም ሆነው ሊታዩ የሚወዱ ሁሉ እንድትገረዙ ግድ አሉአችሁ፥ ነገር ግን ስለ ክርስቶስ መስቀል እንዳይሰደዱ ብቻ ነው።
13Bet net ir patys apipjaustyti nesilaiko įstatymo, o tenori jūsų apipjaustymo, kad galėtų pasigirti jumis.
13በሥጋችሁ እንዲመኩ ልትገረዙ ይወዳሉ እንጂ የተገረዙቱ ራሳቸው እንኳ ሕግን አይጠብቁም።
14Aš nieku nesigirsiu, tik mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus kryžiumi, kuriuo pasaulis man yra nukryžiuotas ir aš pasauliui.
14ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።
15Nes Kristuje Jėzuje nieko nereiškia nei apipjaustymas, nei neapipjaustymas, bet naujas kūrinys.
15በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።
16Visiems, kurie laikysis šios taisyklės, teateinie ramybė ir pasigailėjimas; taip pat ir Dievo Izraeliui!
16በዚህም ሥርዓት በሚመላለሱ ሁሉ ላይ በእግዚአብሔር እስራኤልም ላይ ሰላምና ምሕረት ይሁን።
17Nuo šiol tegul niekas manęs nebevargina, nes savo kūne nešioju Viešpaties Jėzaus žymes.
17እኔ የኢየሱስን ማኅተም በሥጋዬ ተሸክሜአለሁና ከእንግዲህ ወዲህ አንድ ስንኳ አያድክመኝ።
18Mūsų Viešpaties Jėzaus Kristaus malonė tebūna, broliai, su jūsų dvasia! Amen.
18ወንድሞች ሆይ፥ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን። አሜን።