1Taigi aš, kalinys Viešpatyje, raginu jus elgtis, kaip dera jūsų pašaukimui, į kurį esate pašaukti.
1እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤
2Su visu nuolankumu bei romumu, su ištverme pakęsdami vienas kitą meilėje,
2በትሕትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም፤ እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፤
3siekite išsaugoti Dvasios vienybę taikos ryšiais.
3በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።
4Vienas kūnas ir viena Dvasia, kaip ir esate pašaukti vienai pašaukimo vilčiai.
4በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደ ተጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፤
5Vienas Viešpats, vienas tikėjimas, vienas krikštas.
5አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤
6Vienas Dievas ir visų Tėvas, kuris virš visų, per visus ir visuose.
6ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ።
7Bet kiekvienam iš mūsų duota malonė pagal Kristaus dovanos saiką.
7ነገር ግን እንደ ክርስቶስ ስጦታ መጠን ለእያንዳንዳችን ጸጋ ተሰጠን።
8Todėl sakoma: “Pakilęs aukštyn, nusivedė belaisvius ir davė žmonėms dovanų”.
8ስለዚህ። ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ምርኮን ማረከ ለሰዎችም ስጦታን ሰጠ ይላል።
9Ką reiškia “Jis pakilo”, jeigu ne tai, kad Jis pirma ir nusileido į žemesniąsias žemės vietas.
9ወደ ምድር ታችኛ ክፍል ደግሞ ወረደ ማለት ካልሆነ፥ ይህ ወጣ ማለትስ ምን ማለት ነው?
10Tas, kuris nužengė, yra ir Tas, kuris iškilo aukščiau už visus dangus, kad visa užpildytų.
10ይህ የወረደው ሁሉን ይሞላ ዘንድ ከሰማያት ሁሉ በላይ የወጣው ደግሞ ያው ነው።
11Ir Jis paskyrė vienus apaštalais, kitus pranašais, evangelistais, ganytojais ir mokytojais,
11እርሱም አንዳንዶቹ ሐዋርያት፥ ሌሎቹም ነቢያት፥ ሌሎቹም ወንጌልን ሰባኪዎች፥ ሌሎቹም እረኞችና አስተማሪዎች እንዲሆኑ ሰጠ፤
12kad išlavintų šventuosius tarnavimo darbui, Kristaus kūno ugdymui,
12ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት፥ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ፥ ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራትና ለክርስቶስ አካል ሕንጻ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ።
13kol mes visi pasieksime tikėjimo vienybę ir Dievo Sūnaus pažinimą, tobulai subręsime iki Kristaus amžiaus pilnatvės saiko,
14እንደ ስሕተት ሽንገላ ባለ ተንኮል በሰዎችም ማታለል ምክንያት በትምህርት ነፋስ ሁሉ እየተፍገመገምን ወዲያና ወዲህም እየተንሳፈፍን ሕፃናት መሆን ወደ ፊት አይገባንም፥
14kad daugiau nebebūtume kūdikiai, siūbuojami ir nešiojami bet kokio mokymo vėjo, žmonių apgaulės, gudrumo, vedančio į paklydimą,
15ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ፤
15bet, kalbėdami tiesą meilėje, augtume visame kame į Jį, kuris yra galvaKristus.
16ከእርሱም የተነሣ አካል ሁሉ እያንዳንዱ ክፍል በልክ እንደሚሠራ፥ በተሰጠለት በጅማት ሁሉ እየተጋጠመና እየተያያዘ፥ ራሱን በፍቅር ለማነጽ አካሉን ያሳድጋል።
16Iš Jo visas kūnas, suderintas ir stipriai sujungtas įvairių raiščių, pagal savo saiką veikiant kiekvienai daliai, auga, kad ugdytų save meilėje.
17እንግዲህ አሕዛብ ደግሞ በአእምሮአቸው ከንቱነት እንደሚመላለሱ ከእንግዲህ ወዲህ እንዳትመላለሱ እላለሁ በጌታም ሆኜ እመሰክራለሁ።
17Taigi aš liepiu ir įspėju Viešpatyje, kad jūs nebesielgtumėte, kaip elgiasi pagonys dėl savo proto tuštybės.
18እነርሱ ባለማወቃቸው ጠንቅ በልባቸውም ደንዳንነት ጠንቅ ልቡናቸው ጨለመ፥ ከእግዚአብሔርም ሕይወት ራቁ፤
18Jų protas aptemęs, jie atskirti nuo Dievo gyvenimo dėl savo neišmanymo bei širdies užkietėjimo.
19ደንዝዘውም በመመኘት ርኵሰትን ሁሉ ለማድረግ ራሳቸውን ወደ ሴሰኝነት አሳልፈው ሰጡ።
19Jie sustabarėję, pasidavę gašlumui, nepasotinamai daro visus nešvarius darbus.
20እናንተ ግን ክርስቶስን እንደዚህ አልተማራችሁም፤
20Bet jūs ne taip pažinote Kristų!
21በእርግጥ ሰምታችሁታልና፥ እውነትም በኢየሱስ እንዳለ በእርሱ ተምራችኋል፤
21Juk iš Jo girdėjote ir Jame išmokote,nes tiesa yra Jėzuje,
22ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥
22kad privalu atsižadėti senojo žmogaus ankstesnio gyvenimo būdo, žlugdančio apgaulingais geismais,
23በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥
23atsinaujinti savo proto dvasioje
24ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።
24ir apsirengti nauju žmogumi, sutvertu pagal Dievą teisume ir tiesos šventume.
25ስለዚህ ውሸትን አስወግዳችሁ፥ እርስ በርሳችን ብልቶች ሆነናልና እያንዳንዳችሁ ከባልንጀሮቻችሁ ጋር እውነትን ተነጋገሩ።
25Tad, atmetę melą, “kiekvienas tekalba tiesą savo artimui”, nes esame vieni kitų nariai.
26ተቆጡ ኃጢአትንም አታድርጉ፤
26“Rūstaukite ir nenusidėkite”. Tegul saulė nenusileidžia ant jūsų rūstybės!
27በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፥ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት።
27Ir neduokite vietos velniui.
28የሰረቀ ከእንግዲህ ወዲህ አይስረቅ፥ ነገር ግን በዚያ ፈንታ ለጎደለው የሚያካፍለው እንዲኖርለት በገዛ እጆቹ መልካምን እየሠራ ይድከም።
28Kas vogdavo, tegu daugiau nebevagia, bet dirba, darydamas savo rankomis gerus darbus, kad turėtų iš ko padėti stokojančiam.
29ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።
29Joks bjaurus žodis teneišeina iš jūsų lūpų; bet tik tai, kas gera, kas tinka ugdymui ir suteikia malonę klausytojams.
30ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ።
30Ir neliūdinkite Šventosios Dievo Dvasios, kuria esate užantspauduoti atpirkimo dienai.
31መራርነትና ንዴት ቁጣም ጩኸትም መሳደብም ሁሉ ከክፋት ሁሉ ጋር ከእናንተ ዘንድ ይወገድ።
31Tebūna toli nuo jūsų visoks kartėlis, piktumas, rūstybė, riksmai ir keiksmai su visomis piktybėmis.
32እርስ በርሳችሁም ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ፥ እግዚአብሔርም ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ።
32Būkite malonūs, gailestingi, atlaidūs vieni kitiems, kaip ir Dievas Kristuje atleido jums.